Tuesday, March 25, 2014

መታመን በቀድሞ ነው !!

https://www.zehabesha.com/amharic/archives/13847
የሰሞኑ የኪዌት ጉዳይ ሁላችንንም እያነጋገረ ያለ ጉዳይ ነው በተለይ በቅርቡ ከሳውዲ አረብያ የችግር ትኩሳት ትንሽ መብረድ ጋር ተያይዞ  በኪዌት የባለ ስልጣን ልጅ መገደል የወገኔን ችግር   ያብስዋል ብዬ  ነገሩን ትኩረት ሰጥቸው  እየተከታተልኩ ነው :: በጣም ትኩረቴን የሳበው እና የታዘብኩተ  የኪዌት የፓርላማ አባላት ተወያይተው የወሰኑት ጉዳይ ነው ::
The lawmaker stressed the need to oblige housemaids to undergo tests regularly to ensure they are not suffering from any psychological illness. 
.የቤት ውስጥ ሰራተኞች ቅጥር ውደ ኪዌት ሲመጡ የአምሮአቸው ሁኔታ ይጠና ማለታቸው ትክክል ቢሆንም እኔ ግን በትዝብት እና በግርምት ነው የተመለከትኩተ :: ምነው ስንቱን ወገኖቻችንን ሲገድሉ ሲያርዱ ሲያንገላቱ የነሱን የራሳቸውን  አእምሮ ሁኔታ አለማጤናቸው ?? እውነት ትክክል የሆነና ያልሆነ  ነገር ለካ እንደ ሃገሩ ይለያያል እነሱ ሲፈጽሙት እና እኛ ስንፈጽመው የሚሰጠን ስያሜ ለየቅል ነው ለካ :: በአረቡ አለም ስንት ህሊናን የሚያስትና እሚያንገፈገፍ ዘግናኝ ግፍ ተፈፅሞብን እንዳለፈ ቤቱ ይቁጠረው እውነቱን ነው ትልቁ መጽሓፍ ያለው " በራስክ ውስጥ ያለውን ትልቁን ምስሶ የሚአክል ጉድፍ እያለ የወንድምክን ትንሽዋን የአይን ጉድፍ ላውጣ ማለቱ ............" የሚለው  የሚስማማቸው ይመስለኛል::
            ያገራችን  መንገስትም ለአንድ ዜጋው የሚሰጠው  ክበር ሰለሌለ የሚከፍለው ዋጋ የዛኑ ያህል የከፋ ነው:: አንድ ዜጋ በሚፈጥረው ችግር ህብረተሰበን ብሎም አገርን እንደሚጎዳ በቅጡ የተገነዘበው አልመሰለኝም እኔ ሳስበው ችግሩ ሁላችንንም ያካትታል በተለይ መንግስትን!!! " ምቼም መንግስት የሚታመነው በባለፈው ስራው ነው" በተለይ አረብ አገር ባሉ ዜጎቻችን ላይ ሲበደሉ  ሲገደሉ መሬት ለመሬት ሲጎትቱአቸው አሁን ያለው መንግስት ለወገኑ ጥብቅና ሲቆም ሲታገልላቸው መብታቸውን ለማስከበር ደፋ ቀና ሲል አላየንም ከነሱ ጋረ ሆኖ በችግራችን ላይ ችግር ሲጨምርብን እንጂ !!  በየሃገሩ ተበትነው ያሉ ዜጎቻችን አለሁ የሚል  መንግስት ወገን ከሌለ ምኑን መንግስት ሆነልን!!  አገር ውሰጥም ተገብቶ ጭቆናወና ችግሩ እየቀጠለ የሚሄድ ከሆነ አሁንም እንዳየነው ፍልሰቱ መቀጠሉ የማይቀር ነው :: በቅርቡ ከሳውዲ የተመለሱት ወዳገራቸው ገብተው በያቅጣጫው ወደ ውጭ  የተበተኑት ይሄ ያደባባይ ሚስጥር ነው :: እና ለዚች ወገናችን  ከተብደለችው አንጻር ፍርድዋ እንዲቀልላት በጎ አደራጊ ደረጅቶች ወይ ገለሰብ እንድረስላት ::

 



 

No comments:

Post a Comment