Monday, March 5, 2018

የወታደራዊ መረጃ ዋና መምሪያ ሃላፊ ሜ/ ጀነራል ገብሬ ዲላ ከሃላፊነቱ መነሳቱ ታወቀ!!

ESAT
የጸጥታኃይሎች እናማህበረሰብ

የጸጥታ ኃይሎች ዜና (የካቲት 25, 2010 ዓ.ም)

------------------------------------
ከ2000 ዓ.ም ጀምሮ የወታደራዊ መረጃ ዋና መምሪያን ለ10 ተከታታይ አመታት ያክል በሃላፊነት ተመድቦ ዋና መምሪያውን እንደ ፈለገ ሲፈልጥና ሲቆርጥ የነበረው ሜ/ ጀነራል ገብሬ ዲላ በህይወትና በሃገር ሃብት ላይ ከፍተኛ ኪሳራ ማድረሱ ይታወቃል። በተለይ በ1999 ዓ.ም በሱማሊያ እስላሚክ ኮርትን ለመውጋት በሚል ሰበብ ባልተጣና እና በተሳሳተ መረጃ ላይ ተመርኩዞ 43ኛ ክ/ጦርን እየመራ እንዲገባ በማድረግ ሰራዊቱ እንደቅጠል እንዲረግፍ አድርጓል። ክፍለ ጦሩም እንዲደመሰስ በማድረግ ሰራዊቱን በትኖ በመሸሽ የራሱን ህይወት ብቻ ያተረፈ እንደሆነ ይታወቃል። ሜ/ ጀነራል ገብሬ ዲላ ለፈጸመው ክህደት እና ከፍተኛ ጥፋት ተጠያቂ ከሚሆኑት የህወሃት ከፍተኛ መኮንኖች መካከል አንዱ መሆን ሲገባው እሱ ግን ስልጣንን በላይ በላዩ በመደራረብ የወታደራዊ መረጃ ዋና መምሪያ ሃላፊ እስከመሆን የደረሰ ነው።
ጀነራል ገብሬ ዲላ ምንም አይነት ለቦታው የሚመጥን ብቃት ሳይኖረው ወታደራዊ መረጃ ዋና መምሪያን ለ10 ተከታታይ አመታት እንዲመራ የተደረገው ከመከላከያ ኤታ ማዦር ሹም ከጀነራል ሳሞራ የኑስ ጋር በነበረው ቅርብ ወዳጅነት መሆኑን ይነገራል። ስለሆነም በ2000 ዓ.ም ጀነራሉ ወደ ወታደራዊ መረጃ ዋና መምሪያ ሃላፊነት የመጣው ከጀነራል ሳሞራ የኑስ ጋር የነበረውን ቅርብ ግንኙነት እንደ መልካም አጋጣሚ ተጠቅሞ እንደሆነ ጉዳዩን በቅርበት የሚያውቁ አካላት ይገልጻሉ።
የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስተር አቶ መለስ ዜናዊ ሞት ተከትሎ የሳሞራ ስልጣን ከቀን ወደ ቀን እየተሸረሸረ የሚገኝ ሲሆን፣ ለሳሞራ ስልጣን መሸርሸር እንደዋነኛ ምክንያት የተቀመጠው የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ሃልፊ ጌታቸው አሰፋ እንደሆነ ከመከላከያና ከደህንነቱ በየጊዜው አፈትልከው የሚወጡ መረጃዎች በመጠቆም ላይ ናቸው። አቶ ጌታቸው አሰፋ በመከላከያ ሰራዊቱ ውስጥ የሳሞራ የኑስን ስልጣን አስለቅቆ በምትኩ የራሱን ቅርብ ሰዎች በሳሞራ ወንበር ለመተካት ያስችለው ዘንድ የሳሞራን ተከታዮች አስቀድሞ መምታት የሚል ስልት ነድፎ እየተንቀሳቀሰ እንደሚገኝ ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው አካላት እየገለጹ ይገኛሉ።
በዚህም መሰረት በመከላከያ ሰራዊቱ ውስጥ የተፈጠረውን አለመረጋጋት እንደ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም ጀነራል ገብሬ ዲላ ከወታደራዊ መረጃ ዋና መምሪያ ሃላፊነቱ ተነስቶ በምትኩ ለሌላኛው የህወሃት አባል የሆነው ሜ/ ጀነራል አታክልቲ በርሄ ቦታውን እንዲወስድ ተደርጓል። ሜ/ ጀነራል አታክልቲ በርሄ አሁን የወታደራዊ መረጃ ዋና መምሪያ ሃላፊ ሆኖ ከመሾሙ በፊት በመከላከያ የመገናኛና ኢንፎርሜሽን ደህንነት ውስጥ በሃላፊነት ሲሰራ የነበረ ነው። የአሁኑ ተሿሚ ሜጀር ሜ/ ጀነራል አታክልቲ በርሄ ልክ እንደ ገብሬ ዲላ ሁሉ ለቦታው የሚመጥን ምንም አይት መሰረታዊ እውቀት እንደሌለው ጀነራሉን በቅርበት የሚያውቁት በመከላከያ ውስጥ የሚገኙ አካላት ይገልጻሉ። ሜ/ ጀነራል አታክልቲ በርሄ በዘረፋ ከፍተኛ ሃብት ያካበተና በሙስና የተጨማለቀ እንደሆነ ይታወቃል። በእርግጥ በህወሃት ቤት ታማኝነትና አገልጋይነት እንጂ ሙያዊ ብቃትና ልምድ ለሹመትና ሽልማት እንደማያበቃ በ27 ዓመታት የህወሃት ታሪክ መመልከት ተችሏል።

No comments:

Post a Comment