Monday, March 5, 2018

የሕዝቡን ትግል እናግዝ !

የፈረንሳዩ አለም አቀፍ የዜና አውታር የሆነው ራዲዮ FRI። 06:37 ሰዓት ላይ የኢ/ያ ዋና ከተማ አ.አበባ ዛሬ በመንግስት ላይ በተደረገው አድማ ሳቢያ የንግድ ስራዎች በብዙ ቦታዎች ተዘግተውና ሲስተጓጎሉ ውለዋል ብሎናል።በቀጣይ ነገ ምን ሊከሰት እንደሚችል እንከታተል።የአቅማችንም እናድርግ።
ጎበዝ እየተሰራ ያለውን ምእራባውያኑም አውቀውታል።ችግሩ እኛ የምናይበት አተያይና የለመድነው ለዘመናት የተከተልነው የትጥቅ ትግል ስልት ካልሆነ ብለን ሙጥኝ ማለታችን ሲሆን ይህንን እስከመጨረሻው ድረስ ላናየው እንችላለን። ሊቢያን የመንን ሱዳንን ኢራቅን ሶርያን ምን እንዳደረገ እያየ ዘላቂና አዋጭ የተባለውን የትግል ስልት ነው ሕዝብ እየተከተለ ያለው።እድሜ ለተማረ!!! በመንደርና በደደቢት ልጆች ጭንቅላት የሚያስቡ ሰዎች የሚመራ ትግል አይደለም።
ነጮቹንም ግራ ያጋባቸው ቀድሞውን የሚያውቁት በአፍሪካና በአረብ አገራት የሚያዩትና የሚያውቁት የጦር መሳሪያ ትግልን ማየት አለመቻላቸው የበለጠ ምን ሊሆን እንደሚችል መተንበይ የከበዳቸው በመሆኑ እንደቀድሞው እያለሳለሱ መቀጠላቸውን አቁመው ጠንከር ቆንጠጥ የሚያደርግ መግለጫ እያወጡ የቀድሞው አጋራቸው የነበረው ሊባል እንደደረሰ ተረድተው አሰላለፋቸውን ከህዝብ ጎን ማድረግን የመረጡ ይመስላሉ።
ስለዚህ በያለንበት እንደየአቅማችንና በተናበበ መልኩ እየተግባባን የሕዝቡን ትግል እናግዝ።የራሳችንን እየተውንና እያጣጣልን የነጀዋር የነእንትና እያልን ከንቱ መመኘት እናቁም። አሁን ወያኔ ጉሮሮው ተይዞ ነፍስ ውጭ ነፍስ ግቢ ላይ ነው ያለው።ነፍስ እንዳይዘራ ባለው ላይ ማጥበቅ ነው የሚበጀን።

No comments:

Post a Comment