Wednesday, December 4, 2013

በመርካቶ ዛሬ በተነሳው የእሳት አደጋ ዙሪያ አዳዲስ መረጃዎች



               አሁን ለዘ-ሐበሻ የደረሰው መረጃ በመርካቶ አካባቢ በቀድሞው ቦምብ ተራ (የአሁኑ ጆንያ ተራ) የተነሳው ቃጠሎ በመጨረሻም በቁጥጥር ስር ውሏል። በአደጋው ከቀደም ብለን በሰበር ዜና 4 ሰዎች መጎዳታቸውን የዘገብን ሲሆን አሁን ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች ቁጥር ከ10 በላይ ማደጉ ጨምሮ የደረሰን መረጃ ያመለክታል። በአደጋው የደረሰው የንብረት ጥፋት ከፍተኛ ሲሆን እስካሁን በቁጥር የተቀመጠ መረጃ አልተገኘም። ሆኖም በርካታ ሱቆች ግን ወድመዋል።
ቀደም ሲል ከ2 ሰዓት በፊት የዘገብነው ዜና ከዚህ ሥር አለ።
በመርካቶ የተነሳው የእሳት አደጋ ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት ጊዜ አልበረደም። የዘ-ሐበሻ የአዲስ አበባ ዘጋቢዎች እንዳሉት ከሆነ ከቀኑ 8 ሰዓት የተነሳው እሳት ቃጠሎ በእሳት አደጋ ብርጌድ ሊጠፋ ባይችልም 4 ሰዎች በቃጠሎ አደጋ ደርሶባቸው ወደ ተክለሃይማኖት ሆስፒታል ተወስደዋል።
እሳቱ በተለምዶ ቦንብ ተራ (የአሁኑ ጆንያ ተራ) ተብሎ የሚጠራውን አካባቢ ሁሉ መካለሉን፤ በአካባቢው የዘይት ሱቅ በመቃጠሉ የእሳት አደጋው መባበሱን የገለጹት የዘ-ሐበሻ ዘጋቢዎች የእሳት አደጋው ብርጌድ አደጋውን ሊቆጣጠር ያልቻለው በአካባቢው ያሉ ሱቆች በልብስ የተጨናነቁ በመሆናቸው ተብሏል። የእሳት አደጋው ኮልፌ፣ እንዲሁም አራዳ ድረስ በመሄድ የማጥፊያ ውሃዎችን እየቀዳ እንደሚገኝ የገለጹት ምንጮች ለምን መርካቶ አካባቢ ውሃ እንደማይቀዱ የተገለጸ ነገር የለም።
እስካሁን ድረስ ወደ 3 የሚጠጉ የአስፓልት መሸጋገሪያ ያላቸው መንግዶች ስር ያሉ ሱቆች መቃጠላቸውን ያስታወቁት የዘ-ሐበሻ ዘጋቢዎች ከአየር መንገድ እሳቱን ለማጥፋት እግዛ ተገኝቷል ብለዋል። በአካባቢው የ እሳት አደጋውን ተከትሎ ዝርፊያ ሊከሰት ይችላል በሚል ፍራቻ እንዳለ የገለጹት ዘጋቢዎቻችን ነጋዴዎች ንብረታቸውን በግልጽ መኪናዎች በመጫን ከአካባቢው እየሸሹ ነው ብለዋል።
በሌላ በኩል በአካባቢው ያሉ ነጋዴዎች የእሳት አደጋ አጥፊዎች በቅድሚያ እሳቱን ከማጥፋት ይልቅ በገንዘብ እንደሚደራደሩ ያላቸውን ብሶት ለዘ-ሐበሻ ዘጋቢ ተናግረዋል። አንዳንድ ነጋዴዎች እሳቱ አደጋ ሆን ብሎ እንዲባባስ እና ቶሎ እንዳይጠፋ እየተደረገ ያለ ሴራ አለ ብለው የሚያምኑ ሲሆን “መንግስት ቦምብ ተራ(ጆንያ) ተራን ለማፍረስና ለባለሃብት ለመስጠት እየተጠቀመበት ያለው ሴራ ሊሆን ይችላል” ሲሉ አስተያየታቸውን ይሰጣሉ።
ተጨማሪ መረጃ እንደደረሰን እናቀርባለን።
http://www.youtube.com/watch?v=Qt7I30g7Kgs#t=11

No comments:

Post a Comment