Tuesday, December 30, 2014

የኢንተርኔት እና የተንቀሳቃሽ ስልክ መረጃዎች ላይ ጠበቅ ያለ ቁጥጥር የሚያደርግ አዋጅ ተረቀቀ

 ኢሳት ዜና-በሥራ ላይ ያለውን የብሮድካስት አዋጅ የሚሽርና ለመጀመሪያ ጊዜ በኢንተርኔት ድረገጾች እንዲሁም ተንቀሳቃሽ ስልክንበመጠቀም የሚቀርብ የብሮድካስት አገልግሎቶችን  ላይ ጥብቅ ቁጥጥር የሚያደርግ የሚዲያ ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጅቷል፡፡

የኢትዮጵያ የብሮድካስት ባለስልጣን ያዘጋጀውና በዚህ ዓመት ለፓርላማው ቀርቦ ይጸድቃል ተብሎ የሚጠበቀው ይህው የሚዲያ ረቂቅ አዋጅ አሌክትሮኒክስ መገናኛ ብዙሃን ማለትም ራዲዮ፣ቴሌቪዥን፣ የኢንተርኔት ድረገጾች እንዲሁም የሕትመት ሚዲያውን የሚመለከት ነው፡፡ በዚህ አዋጅ ለመጀመሪያ ጊዜ የአንተርኔት ድረገጾች ፈቃድ ማውጣት የግድ መሆኑን ደንግጎአል፡፡
በኢንተርኔት ፣በተንቀሳቃሽ ስልክ ወይም በመሰል የመረጃ መረብ አማካኝነት ለስርጭት የሚቀርብ ማንኛውም ፕሮግራም በአገር አንድነትና ሉአላዊነት ላይ አደጋ የሚጥል ፣በአገር ደህንነት፣ ክብርና ጥቅም ላይ ጉዳት የሚያደርስ ፣የአገር ሚስጢርን የሚገልጽ ፣ አመጽና ጦርነትን የሚቀሰቅስ፣ የሰው ልጆችን ስብዕና ፣ነጻነት ወይንም ስነምግባር የሚጻረር ፣የሌሎችን እምነት የሚያንኳስስ መሆን እንደሌለበት ደንግጎአል፡፡
በተጨማሪም ሥራዎቹ ማንኛውንም የህብረሰተብ ክፍል፣ ብሔር፣ጎሳ፣ቀለም፣ጾታ፣ዘር፣ቋንቋ፣ሃይማኖት፣ማህበራዊ አመጣጥ፣ ወይንም ሌላ መሰል አቋምንና ክብርን የሚነካ ወይም የሚያዋርድ፣ በህዝቦችና በሃይማኖቶች መካከል የእርስ በእርስ ግጭት የሚቀሰቅስ ወይንም ጥላቻ የሚያስፋፋ፣ የግለሰብን ስም የሚያጠፋ፣፣ለአካለ መጠን ያልደረሱ ልጆችን አመለካከት ስሜት የሚጎዳና ወደአልተፈለገ አቅጣጫ እንዲያዘነብሉ የሚገፋፋ፣ የህብረሰተቡን ሞራል የሚጥስ ወይንም በሕግ የተከለከለ ማንኛውንም ድርጊት የሚፈጽም መሆን የለበትም ይላል፡፡
ተጠያቂነትም በተመለከተ ረቂቅ አዋጁ እንዳሰፈረው በኢንተርኔት ፣በተንቀሳቃሽ ስልክ ወይም በመሰል መረጃ መረብ አማካይነት የቀረበ ፕሮግራም ለሚያስከትለው ማንኛውም የወንጀል ድርጊት ወይም የፍትሐብሄር ጉዳት የፕሮግራሙ ሃላፊና የብሮድካስት አገልግሎት ሰጪው በአንድነት ተጠያቂ ይሆናሉ ይላል፡፡
በኢንተርኔት ፣በተንቀሳቃሽ ስልክ ወይም በመሰል መረጃ መረብ አማካይነት የቀረበ ፕሮግራምን ቁጥጥርን በተመለከተ ከህብረተሰቡ በቅሬታ መልክ የሚቀርቡ አቤቱታዎችን የመመርመር፣ተቆጣጣሪ የመመደብ ስልጣን ወደፊት ለሚቋቋመው ባለስልጣን መ/ቤት ሃላፊነቱን ይሰጣል፡፡
ረቂቅ አዋጁ የቴሌቪዥንን ከአናሎግ ወደዲጂታል ሽግግርን ለማቀላጠፍና የግል ቴሌቪዥን ለመፍቀድ ይረዳል ተብሎአል፡፡ በዚህ ረቂቅ አዋጅ መሰረት ተጠሪነቱ ለጠ/ሚኒስትሩ የሆነ የኢትዮጵያ የሚዲያ ባለስልጣን የሚባል መ/ቤት ይቋቋማል፡፡
የብሮድካስት አግልግሎት የሚመራበትን ሥርዓት ለመደንገግ ከ15 ዓመታት በፊት የወጣው አዋጅ ቁጥር 178/1991 የግል ቴሌቬዥን ጣቢያ ፈቃድ ለግል ባለሃብቶች የፈቀደ ቢሆንም ይህ ተግባራዊ ሳይሆን አዋጁ በቁጥር 533/1999 የተሻሻለ መሆኑ ይታወቃል፡፡ በተሸሻለውም አዋጅ ቢሆን የግል ቴሌቭዥን ጣቢያ  የተፈቀደ ቢሆንም ኢህአዴግ መራሹ መንግስት ኢትዮጵያ ለዚህ ደረጃ ገና አልበቃችም በማለት አዋጁ እንዳይፈጸም እስካሁን ድረስ መከልከሉ የሚታወቅ ነው፡፡

የባህር ዳር መስዋዕትነት የማይቀረዉ ድል ዋስትና ነዉ

ወያኔ በየአመቱ ህዳር ወር መጨረሻ ላይ የኢትዮጵያን ብሄር ብረሰቦች ሰብስቦ ዘፈን የሚያስዘፍንበትን በዐል ሲያከብር በተደጋጋሚ ከሚያሳማቸዉ መፈክሮች አንዱ የብሄር ብሄረሰቦች መብትና እኩልነት በህገመንግስታችን ተከበረ የሚል እጅግ በጣም አሳሳች የሆነ መፈክር ነዉ። በእርግጥም ወያኔ ለይስሙላ ወረቀት ላይ ያሰፈረዉ ህገ መንግስት መግቢያዉ ላይ “እኛ የኢትዮጵያ ብሄሮች፤ ብህረሰቦች፤ ህዝቦች በነጻ ፍላጎታችን የህግ የበላይነትና በራሳችን ፍላጎት ላይ የተመሰረተ አንድ የፖለቲካ ማህበረሰብ በጋራ ለመገንባት ቆርጠን ተነስተናል” ይላል። መቼም ይህ ምንም በማያሻማ መልኩ ቁልጭ ብሎ የተቀመጠ ህገ መንግስታዊ አንቀጽ ሌላ ትርጉም ካልሰጡት በቀር የአማራንም ህዝብ ያጠቃልላል የሚል ሙሉ እምነት አለን። በዚህ ደግሞ የአማራን ክልል የማስተዳድረዉ እኔ ነኝ ባዩ ባዕዴንም የሚስማማ ይመስለናል። በተግባር ሲታይ ግን ይህ የወያኔ ህገ መንግስት ላይ ህዝብና መንግስት የሚተዳደሩበት ህግ ቀርቶ ህገ አራዊት እንኳን አይመስልም። ምክንያቱም በህገ አራዊት አሰራር ተመሳሳይ ዝሪያ ያላቸዉና በአ ያላቸዉ የዱር አራዊት ይከባበራሉ እንጂ አንዱ ሌላዉን አያጠፋም። ለምሳሌ አንበሳና አንበሳ ይረዳዳሉ ወይም አብረዉ አደን ይወጣሉ እንጂ እርስ በርስ አይተላለቁም፤ ነብርና አንበሳም ቢሆኑ በተገናኙ ቁጥር ተከባብረዉ ይተላለፋሉ እንጂ አንደ ወያኔ ብጤያቸዉን ባዩ ቁጥር አያጠቁም ወይም አይገድሉም።
ወረቀት ላይ የሰፈረዉን የወያኔ ህገ መንግስት የተመለከተ ሰዉ ኢትዮጵያ ዉስጥ ዜጎች መብታቸዉና ነጻነታቸዉ ተከብሮ የሚኖሩ ሊመስለዉ ይችላል። በእርግጥም ይመስላል። ምክንያቱም የወያኔ ህገ መንግስት ችግሩ አጻጻፉ ላይ ወይም ይዘቱ ላይ ሳይሆን በተግባር አተራጓጎሙ ላይ ነዉ። በ1987 ዓም የፀደቀዉ የወያኔ ህገ መንግስት በተግባር ሲታይ ብሄሮች፤ ብህረሰቦችና ህዝቦች የሚለዉ ቦታ ደብዛዉ ጠፍቶ ሁሉም ነገር ወያኔ ወይም ህወሓት በሚለዉ ቃል ተተክቷል፤ ወይም ሁሉም የአገራችን ብሄር ብሄረሰቦች ተጨፍለቀዉ የትግራይ ልህቃን ወይም የህወሓት ሎሌዎችና ተላላኪዎች ሆነዋል። ለዚህ ነዉ አገራችን ኢትዮጵያ ወያኔ ያሰኘዉን የሚያዝባት የኢትዮጵያ ህዝብ ደግሞ አንገቱን ደፍቶ የሚታዘዝባት አገር የሆነችዉ።
ሌላዉ ወያኔ ህገ መንግስቱ ዉስጥ አስፍሮ በየቀኑ እንደቤቱ ዉስጥ ምንጣፍ ከሚረግጣቸዉ ህገ መንግስታዊ አንቀጾች ዉስጥ አንዱ አንቀጽ 30 ንዑስ አንቀጽ አንድ ነዉ። ይህ አንቀጽ ማንኛዉም ሰዉ ከሌሎች ጋር በመሆን መሳሪያ ሳይዝ በሠላም የመሰብሰብና ሠላማዊ ሠልፍ የማድረግ ነጻነትና አቤቱታ የማቅረብ ሙሉ መብት አለዉ ይላል። ሆኖም የዚህን አንቀጽ ሙሉ ቃል ከወያኔ የየቀኑ አረመኔነት ጋር ስናነጻጽር አንቀጹ የተጻፈበትን ወረቀት ያክል እንኳን ክብደት የለዉም። ይህንን ደግሞ የኢትዮጵያ ህዝብ ሠላማዊ ሠልፍ ባደረገባቸዉ ቦታዎች ሁሉ ወያኔ በተከታታይ በወሰዳቸዉ አረመኔያዊ እርምጃዎችና በፈጸማቸዉ ሰቆቃዎች ተመልክተናል። ለምሳሌ ባለፈዉ አመት አምቦ ዉስጥ አሁን ከሰሞኑ ደግሞ ባህርዳር ዉስጥ ህገ መንግስታዊ መብታቸዉን ተጠቅመዉ ጥያቀያቸዉን ሠላማዊ ሰልፍ በማድረግ ያቀረቡ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸዉ ህፃናት፤ ወጣቶች፤ አዋቅዎች ወንዶችና ሴቶች በአግዓዚ ነብሰ ገዳዮች ጥይት ተጨፍጭፈዋል።
ወያኔ በተደጋጋሚ ሠላም … ሠላም እያለ በአፉ ይናገር አንጂ ወያኔን ከሰላም ጋር የሚያገናኘዉም ሆነ ወያኔ ስለ ሰለም የሚያዉቀዉ ምንም ነገር የለም። እዉነቱን ለመናገር ኢትዮጵያ ዉስጥ ሠላማዊ ሠልፈኞችን የሚገድል፤ ሠላለማዊ ዜጋን አስሮ የሚደበድብና የሠላም መንገዶችን ሁሉ ቅርቅር አድረጎ የዘጋዉ ወያኔ ብቻ ነዉ። ሌላዉ ቀርቶ ወያኔ የሚያስበዉ፤ የሚያቅደዉና ዕቅዱን ወደ ተግባር የሚለዉጠዉ ከህዝብ ፈቃድና ፍላጎት ዉጭ ስለሆነ ልማት ብሎ የሚጀምራቸዉ ፕሮጀክቶች እንኳን የህዝብን ሠላም የሚያናጉና የሠላማዊ ዜጎችን ህይወት የሚቀጥፉ ጅምሮች ናቸዉ። ከሰሞኑ ደግሞ ባህር ዳር ዉስጥ እየታየ ያለዉ ህዝባዊ ቁጣ የዚሁ ወያኔ ልማት እያለ የቀሰቀሰዉ ህዝባዊ እሳት ዉጤት ነዉ።
ወያኔ እራሱን ልማታዊ መንግስት እያለ እየጠራ በሚወስዳቸዉ እርምጃዎች ሁሉ ከህዝብ ጋር መጋጨት ከጀመረ አመታት ተቆጥረዋል። ደቡብ ኦሞ ዉስጥ ሙርሲዎች በልማት ስም ከመሬታቸዉ ተፈናቅለዋል፤ አንፈናቅለም ብለዉ የተፋጠጡት ደግሞ በግፍ ተጨፍጭፈዋል። ታሪካዊዉ ዋልድባ ገዳም ዉስጥ ገዳም አለም በቃኝ ያሉ ሰዎች መኖሪያ አንጂ የእርሻ ቦታ አይደለም ብለዉ የተናገሩ መነኮሳት ቆባቸዉን አንደደፉ በቆመጥና በሰደፍ ተደብድበዋል። ጋምቤላና አፋር ዉስጥም በልማት ስም ከመሬታችን አታፈናቅሉን ብለዉ አቤቱታ ያቀረቡ ገበሬዎች ታስረዋል፤ ተግዘዋል ተገድለዋል። ለመሆኑ ወያኔ ልማት ብሎ አንድ ፕሮጀክት በጀመረ ቁጥር ህዝብን የሚያግዝና የሚገድል ከሆነ ልማቱ የሚታቀደዉ ለማነዉ? በልማቱስ ተጠቃሚ የሚሆነዉ ማነዉ?
በያዝነዉ ታህሳስ ወር መግቢያ ላይ ባህር ዳር ዉስጥ የአራት ሰላማዊ ዜጎችን ህይወት የቀጠፈዉና አለም በቃኝ ብለዉ ለፈጣሪያቸዉ ያደሩትን መነኩሴ ጨምሮ ለአያሌ ሠላማዊ ዜጎች መቁሰልና መታሰር ምክንያት የሆነዉ ይሄዉ ወያኔ በልማት ስም የጀመረዉና የአካባቢዉን ህዝብ ፍላጎት ያላካተተዉ የወያኔ ፀረ ህዝብና ፀረ አገር እርምጃ ነዉ። በእርግጥም አሁንም ድረስ ያልበረደዉ የባህር ዳሩ ህዝባዊ ተቃዉሞ የተቀሰቀሰዉ ወያኔ የባህር ዳርና የአካባቢዉ ህብረተሰብ የጥምቀት በዐል የሚያከብርበትንና የቤ/ክርስቲያን ንብረት የሆነዉን የቅዱስ ታቦት ማደሪያ ቦታ መንገድና ሱቅ እሰራለሁ ብሎ ማፈራረስ በመጀመሩ ነዉ።
ይህ በልማት ስም ሐይማኖታዊ የማመለኪያ ቦታን የማፈራረስና የቤ/ክርስቲያንን መሬት የመቀማት ሴራ የተዉጠነጠነዉ በወያኔ ቢሆንም የወያኔ ተላላኪ በመሆን ይህንን ከፍተኛ ወንጀል በገዛ ወገኖቹና ለጥቅሙ ቆሜያለሁ በሚለዉ ህብረተሰብ ላይ የሚያሰፈጸመዉ ግን ባዕዴን ነዉ። ባዕዴን ከዚህ ቀደምም በተከታታይ እንደታየዉ አማራዉ ከተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች በግፍ ሲባረርና ሲፈናቀል አፉን ዘግቶ የተመለከተና የአማራን ህዝብ ጥቅምና ፍላጎት ለወያኔ አሳልፎ የሰጠ ከሃዲ ድርጅት ነዉ። ባዕዴን ነኝ ብሎ እንደሚናገረዉ በእርግጥም ለአማራ ህዝብ መብትና ነጻነት መከበር የቆመ ድርጅት ቢሆን ኖሮ የለየለት የአማራ ህዝብ ጠላት የሆነዉ ህወሓት አያገባዉ ገብቶ በአማራ ህዝብ ጉዳይ ላይ ሲፈተፍት ዝም ብሎ አይመለከትም ነበር።
ዘረኞቹ የወያኔ መሪዎች የኢትዮጵያን ህዝብ ታሪክና አንድነት ብቻ ሳይሆን ባህሉን ፤ወጉንና ሐይማኖቱን ጭምር እንዳልነበረ ለማድረግ ያላደረጉት ነገር የለም። የኢትዮጵያን ኦርቶዶክስ ቤ/ክኢርሰቲያን ጳጳስ አንስተዉ ቅዱስ መንበራቸዉን እጁ በደም ለተጨማለቀ ካድሬ በመስጠት ጥንታዊት ቤ/ክርስቲያናችንን ለሁለት አንድትከፈል አድርገዋል። ይህ ሁሉ አልበቃ ብሏቸዉ ከሰሞኑ ባህርዳር ዉስጥ ህዝብ ጥምቀተ በዐል የሚያከብርበትንና የቅዱስ ታቦት ማደሪያ የሆነዉን ቦታ ከቤ/ክርስቲያን ቀምተዉ የንግድ ቦታ ለማድረግ ሞክረዋል። የእስልምና እምነት ተከታዮችን በተመለከተም ህጋዊዉን መጂሊስ አፍርሰዉ በእነሱ ፍላጎት ብቻ የሚመራ አሻንጉሊት መጂሊስ በማቋቋማቸዉ ከህዝበ ሙስሊሙ ጋር የፈጠሩት ግጭት ዛሬም ድረስ እንደተቀጣጠለ ነዉ።
የወያኔ ነብሰ ገዳዮች አዲስ አበባ፤ አምቦ፤ ደቡብ ኦሞ፤ ጋምቤላ፤ አፋርና አሁን በቅርቡ ደግሞ ባ/ህርዳር ዉስጥ በሰላማዊ ዜጎች ላይ የፈጸሙት አረመኔያዊ ጭፍጨፋ እነዚህ ሰዎች ስራቸዉ አገር መምራት ነዉ ወይስ ህዝበን እያደኑ መግደል ነዉ የሚያሰኝ ነዉ። በእርግጥም ወያኔ እስከዛሬ የገደላቸዉን ሰዎችና ሰዎቹን የገደለበትን ምክንያት ስንመለከት የወያኔ የሙሉ ግዜ ስራ አገር መምራት ሳይሆን ህዝብን ምክንያት እየፈከገ መጨፍጨፍ መሆኑን ያረጋግጥልናል። በተለይ በቅርቡ ባህርዳር ዉስጥ አለም በቃኝ ብለዉ ገዳም የገቡትን መነኩሴ በጥይት መትተዉ ማቁሰላቸዉን ስንመለከት ወያኔዎች የገነቡትን ዘረኛ ስርዐት ዕድሜ ለማራዘም ምንም ነገር ከማድረግ ወደ ኋላ እንደማይሉ በግልጽ ያመለክታል።
አለማችን ዛሬም ብዙ ጨቋኝ መሪዎች የሚኖሩባት የአምባገነኖች መድረክ ናት፤ ሆኖም ህዝብ በተቃወማቸዉና በሠላማዊ ሠልፍ ቁጥዉን በገለጸ ቁጥር እንደ ወያኔ ያለ ምንም ማመንታት ሀዝብን በጥይት የሚጨፈጭፍ አረመኔያዊ አገዛዝ የለም። እዚህ ላይ አንድ ፍጹም ግራ የሚያጋባ ነገር አለ፤ እሱም ወያኔ ሠላማዊ ሰለፍኞችን በጥይት የሚጨፈጭፈዉ ሆን ብሎ ህዝብን የሚያስቆጡና የሚያነሳሱ ፀር ህዝብና ፀረ አገር እርምጃዎችን እየወሰደ ነዉ። ለምሳሌ ብዙዎቹን የወያኔ ጭፍጨፋዎች ትተን ሰሞኑን ባህርዳር ላይ የደረሰዉን እልቂት ብቻ ብንመለከት ህዝባዊ ቁጣዉ የተቀሰቀሰዉ ወያኔ ካልጠፋ ቦታ የቅዱስ ታቦት ማደሪያ የሆነዉን ቦታ አፍርሶ የሸቀጣ ሸቀጥ መሸጯ ቦታ ለማድረግ በመሞከሩ ነዉ።
የኢትዮጵያ ህዝብ ሀይማኖቱ ሲነካ ወይም ሀይማኖታዊ ስርዐቱና ልምዱ ጣልቃ ሲገባባቸዉ እጅግ በጣም የሚቆጣና ተኝቶ የማያድር ህዝብ ነዉ። ለምሳሌ የኢትዮጵያ ህዝብ ቤ/ክርስቲያኑ አላግባብ ከፈረሰበትና ጥምቀት፤ ገና፤ ፋሲካ፤ ቡሄ፤ ቅዱስ ዮሐንስና ደመራን የመሳሰሉ ሀይማኖታዊ ስርዐቶቹንና ልምዶቹን በለመደበት ግዜና ቦታ እንዳያከብር ከተከለከለ፤ በከልካዮቹ ላይ መነሳት ብቻ ሳይሆን እነሱን ከማጥፋት የማይመለስ ህዝብ ነዉ። ዛሬ አገር ቤትም ሆነ በዉጭ አገሮች የሚኖረዉ ኢትዮጵያዊ አይኖቹን ወደ ባህር ዳር ያዞረዉና እኛም ዉቧ የባህርዳር ከተማ የወያኔ መጨረሻ የተጀመረባት ከተማ ናት ብለን አፋችንን ሞልተን የምንናገረዉ ይህንን ስለምንረዳ ነዉ።
የኢትዮጵያ ህዝብ የወያኔን ግፍና መከራ ከ23 አመታት በላይ ተሸክሞ ኖሯል። በእነዚህ ሃያ ሦስት አመታት ዉስጥ ሠላማዊ ኢትዮጵያዉያን በየመንገዱና በየአደባባዩ እንደ ዱር እንስሳ እየታደኑ ተገድለዋል። አዲስ አበባ፤ አምቦ፤ አዋሳ፤ደቡብ ኦሞ፤ አፋር፤ ጋምቤላ፤ አርሲ ገደብ አሳሳና ኮፈሌ ዉስጥ አሁን ከሰሞኑ ደግሞ ባህር ዳር ዉስጥ የንጹህ ኢትዮጵያዉያን ደም በግፍ እንደ ጎርፍ ሲፈስ ተመለክተናል። ወያኔንና ዘረኛ ስርዐቱን አስወግደን ኢትዮጵያን የህዝቦቿ አገር ካላደርግናት በቀር ወያኔ ስራዉ መግደል ነዉና እሱ እየገደለ እኛም የእያንዳንዳችን ተራ እስኪደርስ ድረስ ወያኔ የገደለዉን እየቀበርን መኖራችን የማይቀር ነዉ። የኢትዮጵያ ህዝብ ሆይ! ያለህ አማራጭ አንድ ብቻ ነዉ፤ እሱም ሁሌ እየሞትክና እየቀበርክ ከምትኖር ከወያኔ ጋር ፉት ለፊት ተጋፍጠህ እንዳባቶችህ የክብር ሞት ሙትና ለልጆችህና ለልጅ ልጆችህ ህይወት ሁንላቸዉ። አንተ በአንድነት ተነስተህ ፊትህን ወደ ወያኔ ካዞርክ ወያኔ እንደ ጉም በንኖ የሚጠፋ ገለባ ነዉ። ወያኔ እየረገጠ የሚገዛህና የሚገድልህ አንተኑ እንደ ሀይል በመጠቀም ነዉና ለወያኔ አልገዛም በል። ከሁሉም በላይ ደግሞ በዚህ በያዝነዉ የሞትና የሽረት አመት ወያኔን ለማስወገድ ከዉጭም ከዉስጥም በሚደረገዉ ትግል ዉስጥ ድርሻህን ተወጣ። ድል ምንግዜም ያንተ ነዉና . . . . አይዞህ፤ በርታ ዝመት

Monday, December 29, 2014

“አሁን ባለው ሁኔታ ምርጫው ቅርጫ የሚሆን አይመስልም” – ዶ/ር መረራ ጉዲና አዲስ ቃለምልልስ


(ዘ-ሐበሻ) ዶ/ር መረራ ጉዲና ዛሬ ማምሻውን በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ከላስቬጋስ ኔቫዳ ለሚሰራጨው ሕብር ራድዮ በሰጡት ቃለምልልስ የዘንድሮው ምርጫ አሁን ባለው ሁኔታ ምርጫ ሳይሆን ቅርጫም የሚሆን አይመስልም አሉ:: ዶ/ሩ ሰሞኑን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የማስተማር ሥራቸው ተባረዋል ስለተባለው ዜናም በቃለምልልሱ ላይ አንስተዋል::
ሙሉ ቃለምልልሱን ቀጥሎ ካለው ቭዲዮ ይመልከቱ::








Tuesday, December 23, 2014

Ethiopian pilots very likely to have landed at Eritrea-held Assab Port: source

WASHINGTON, DC - An Ethiopian pilot and two of his crew members defected to Eritrea flying an Mi-35 combat helicopter, the state television announced on Monday.

The pilots were based in the eastern city of Dire Dawa and they executed their plan during what the state-owned TV called a "routine flight training." The announcement came in after days of massive aerial search across northeastern Ethiopia.

The crew members were Captain Samuel Giday, Lt. Bililign Desalegn, and flight technician Tsegaberhan Giday. It was not known whether the pilot and technician are siblings.

The TV didn't specify where in Eritrea the pilot landed the helicopter, but an Ethiopian Air Force source cited the Port of Assab as the most likely place of landing the aircraft.

The $25 million Mi-35M helicopter integrates modern high-precision weaponry for destroying ground-based armoured targets and providing air support for ground missions, according to one source related to selling the Russian-made helicopter.

"It is a huge loss for the government," the source said, adding that "since Ethiopia and Eritrea have no diplomatic ties, Addis Ababa may seek the help of neighboring Sudan to retrieve the multi-purpose combat helicopter."

Earlier this year, eight Air Force men defected to Eritrea where they reportedly joined Ethiopian rebel groups.

Eritrea gets 2nd Mi-35 combat helicopter

It is the second time that Eritrea has acquired Mi-35 helicopter from Ethiopia.

"During the 1998-2000 Ethiopia-Eritrea War, an Ethiopian pilot landed his Mi-35 helicopter in an Eritrean territory, claiming that his copter was attacked and damaged. He was rescued but the helicopter was left there intact. The next day, the Eritreans sought the help of an Ethiopan pilot who was living in Asmara as a political asylee, and flew the helicopter to Asmara, signifying that it had no damage."

The Air Force source, who was speaking to Ethiomedia on condition of anonymity, said it was a mystery why the Ethiopian pilot chose to leave an important war machine in the hand of the enemy instead of destroying it.

First, he landed the helicopter in an enemy territory, though it was not damaged. Second, the rule of war dictates that war machines be destroyed lest the enemy makes use of them. They failed to do that. This makes it a mystery: either the pilots were not very well qualified to do the job, or else there was a conspiracy of passing an important war machine to the hand of the enemy.

The latter may sound far-fetched but it should be remembered that Ethiopia was in the hand of the late Prime Minister Meles Zenawi, an ultra Eritrean nationalist mercenary who kept a low profile until he wiped out his Ethiopian critics and sabotaged the war victory over Eritrea.

Today Eritrea is a pariah state, with its citizens fleeing in every direction to escape the harsh rule of President Isaias Afewerki. But the Eritrean desert has also an oasis for Ethiopian Air Force men who desperately seek a refuge from the choking political repression at home.

Friday, December 19, 2014

አምስት ሰዎች ሲቆስሉ ሁለት ሞተዋል፣ የባህርዳር ህዝብ አደባባይ በመውጣት ተቃውሞውን በማሰማት ላይ ነው

ባህርዳር ህዝብ ተቃውሞውን እየተቀላቀለ ነው

• አምስት ሰዎች ሲቆስሉ ሁለት ሞተዋል
Bahir Dar protest
በባህርዳር የተቃውሞ ሰልፍ በወያኔ ታጣቂዎች ድብደባ ከተፈጸመባቸው ውስጥ አንዱ
(ነገረ-ኢትዮጵያ)  ባህርዳር ከተማ ላይ የተነሳውን የህዝብ ተቃውሞ ፖሊስ በኃይል ለመበተን ጥረት እያደረ ቢሆንም ህዝቡ በብዛት ተቃውሞውን እየተቀላቀለ መሆኑን ከቦታው የደረሰን መረጃ ያመለክታል፡፡ ፖሊስ በተኮሰው ጥይት ሁለት ወጣቶች ህይወታቸው ያለፈ ሲሆን ሌሎች አምስት ያህል ወጣቶች እንደቆሰሉ ተገልጾአል፡፡
በአሁኑ ወቅት ከቀበሌ 10 አባይ ማዶ ያለው መንገድ ተቃውሞውን በተቀላቀለው ህዝብ የተዘጋ ሲሆን ወደ ጎንደር የሚወስደው መንገድም መዘጋቱ ታውቋል፡፡ የቀበሌ 8፣ 10ና 11 ነዋሪዎች እንዲሁም የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ተቃውሞውን እየተቀላቀሉ ነው ተብሏል፡፡ የአፈ ጉባኤ ጽ/ቤት አካባቢም በርካታ ህዝብ የተገኘ ቢሆንም ርዕሰ መስተዳደሩን ጨምሮ ሌሎች ባለስልጣናት የሉም እንደተባሉ ገልጸውልናል፡፡
Bahir Dar demonstration
በባህርዳር የተቃውሞ ሰልፍ በወያኔ ታጣቂዎች በጥይት የተመቱ መነኩሴ
————————-
(ነገረ-ኢትዮጵያ) ባህርዳር ከተማ ውስጥ 04 ቀበሌ እየተባለ የሚጠራው አካባቢ የሚገኘውን የጥምቀት ታቦት ማደሪያ ለባለሀብት ይሰጣል መባሉን ተከትሎ ህዝቡ አደባባይ ወጥቶ ተቃውሞውን በማሰማት ላይ መሆኑን የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች ገለጸዋል፡፡Protest in Bahirdar, Ethiopia
ምንጮቹ እንደገለጹት እጅግ በርካታ ህዝብ አደባባይ የወጣ ሲሆን፣ ሰልፈኞቹ በእምነታቸው እየተደረገባቸው የሚገኙትን ጣልቃ ገብነቶችና ሌሎቹንም ስርዓቱ እየፈጠራቸው የሚገኙትን ችግሮች የሚቃወሙ መፈክሮች እያሰሙ ይገኛሉ፡፡
የአማራ ክልል አስተዳደር የቤተ ክርስቲያን ንብረት የሆነውን የታቦት ማደሪያ ለመንገድና ለጥቃቅንና አነስተኛ ሱቆች መስሪያ እንዲነጠቅ ማዘዙን ተከትሎ በቤተ ክርስቲያን የተጠራው ተቃውሞ አሁንም ድረስ እንደቀጠለ መሆኑን የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች ገልጸዋል፡፡ ከታቦት ማደሪያው 9 ሜትር ገብቶ መንገድ እንዲሰራ እንዲሁም ቀሪው ለጥቃቅንና አነስተኛ ሱቆች እንዲሰጥ አስተዳደሩ ማዘዙን ተከትሎ ታቦት ማደሪያውን ከነገ ህዳር 10/2007 ዓ.ም ጀምሮ ሊፈርስ እንደነበር መረጃው የደረሳት ቤተ ክርስቲያን ለህዝበ ክርስቲያኑ አስቸኳይ ጥሪ ማስተላለፏ ታውቋል፡፡
ህዝቡም ‹‹በቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ተገናኝተን በእግዚያብሄር ስም በአስቸኳይ ጠርተንዎታል›› በሚል በቀረበለት ጥሪ መሰረት ዛሬ ጠዋት ተቃውሞውን የጀመረ ሲሆን አሁንም ድረስ እንደቀጠለ ተገልጾአል፡፡ ህዝቡ ቀበሌ 10 በሚገኘው አዲሱ ምክር ቤት እንዲሁም በዚሁ ቀበሌ በሚገኘው የቀድሞው ምክር ቤት በመገኘት ተቃውሞውን እየገለጸ ይገኛል፡፡ በተለይ በአዲሱ ምክር ቤት ተገኝቶ ተቃውሞውን እያሰማ የሚገኘውን ህዝብ በኃይል ለመበተን ጥረት እየተደረገ እንደሚገኝ ከቦታው የደረሰን መረጃ ያመለክታል፡፡

ቴዲ አፍሮ ፓስፖርቱ ተመለሰለት

(ዘሐበሻ) ላለፉት ፫ ሳምንታት ከሃገር እንዳይወጣ ታግዶ የነበረው ድምጻዊ ቴዲ አፍሮ ፓስፖርቱ ተመለሰለት። ፍርድ ቤት ሳያዝ ማን እንደከለከለው ሳይታወቅ በድህነንቶች ፓስፖርቱን ተቀምቶ ሲጉላላ የነበረው ቴዲ ኣፍሮ በዚህ የተነሳ በፊንላንድ እና በሆላንድ ኮንሰርቱን ለመሰረዝና የ፫፪ ሺ ዩሮ ኪሳራ ሊደርስበት ችሉዋል።
teddy afro
የመንግስት መገናኛ ብዙሃን በተለይም የስርዓቱ ኣፈቀላጤ የሆኑ ሚዲያዎች ቴዲ ከሃገር አንዳይወጣ የተከለከለው ከዓመታት በፊት ይነዳት የነበረችው መኪና ታክስ ባለመክፈሉ በተከሰሰበት ክስ ነው ቢሉም ቴዲ በዚህ ክስ በዋስ የወጣና ክስም ያልተመሰረተበት ከመሆኑም በላይ ፍርድ ቤቱ ከሃገር አንዲወጣ ፈቃድ የሰጠበትን ወረቀት መያዙ ጉዳዩን ፖለቲካዊ ይዘት አንዲኖረው ኣድርጉዋል።
ቴዲ ፓስፖርቱን የያዙበት ደህንነቶች ትናንት የለቀቁለት በመሆኑ ምናልባትም ችግር ካልገጠመው ወደ ኣውሮፓ ሊጉዋዝ ይችላል ተብሉዋል፥፥ ቴዲ በኣውሮፓ ኦስሎ ነገ የሙዚቃ ኮንሰርቱንም ያቀርባል ተብሎ ይጠበቃል። የቴዲ ባንድ ከሆላንድ ወደ ኦስሎ ትናንት ያመሩ ሲሆን በነገው ዕለት የሚደረገው ኮንሰርትም በጉጉት እንደሚጠበቅ ከኖርዌይ ለዘሐበሻ የደረሰው መረጃ ያመለክታል።

Wednesday, December 17, 2014

የኢትዮጵያን ዲሞክራሲ ለመዉለድ ስንት ዘመን ይፈጃል?

ምርጫ ደርሷል አይደል? ለዛ መሆን አለበት በአንድ በኩል EBC ‘ምርጫ ቦርድ ለምርጫ አስፈፃሚዎች ስልጠና ሰጠ … ኮሮጆ አሰራጨ’… ሌሎች መገናኛ ብዙሃን ደግሞ ‘ምናምን የሚባል ፓርቲ ሰልፍ ጠራ’ … ‘የነእከሌ ፓርቲ ትየንተ ህዝብ በፖሊስ ሃይል በሃል ተበተነ’ ….. ዱዱዱዳ…እንዲያም እንዲህም የሚሉ ወሬዎች መስማት ከመሰንበቻዉ የተለመደ ሆኗል፡፡
እኛ ሃገር ስለምርጫ አምስት ዓመት እየጠበቁ ማዉራት የተለመደ ተከታታይ ድራማ (series TV show) ይመስላል… የመጪዉ ግንቦት አምተኛዉ ምእራፍ (Season 5) መሆኑ ነዉ ማለት ነዉ? ቂቂቂቂ….! እኔ የምለዉ ግን ለይመሰል ብቻ ምርጫ ማድረግ ምን ይጠቅማል? መጨረሻዉን ቀድመዉ ያወቁትን ፊልም ማየት ወይ ‘ልብ አንጠልጣይ’ የተባለ ልብ ወለድ መፃፍ ማንበብ ጊዜ ማሳለፊያ አልያም የደራሲዉን ችሎታ ለመገምገም ካለሆነ በቀር ምኑ ይነሽጣል? እሺ አንድ ሁለቴ እያወቁ መሸወድ ያለ ነዉና ምን አይደል እንበል…. አመስቴ ስሆንስ? አራዶቹ  ቢሰሙ ‘አይከይፈፍም’ ይሉናል ከምር ኩሸት ይሆናል! ልጆች ሆነን ‘ክስክስ’ የምንለዉ አይነት አክሽን ፊልም ስናይ ‘አክተሩ’ አይሞትም ምናመን ብለንና አምነን አሳምነን ፊል ማየት እንጀምራለን እዉነትም ፊልሙ ሲገባደድ አክተሩ ጠላቶቹን ያሸንፋል በቃ አይሞትም…. የኛም ሃገር ምርጫም ልክ እንደዛዉ ነዉ….. መሪ ተዋናዩ የማይሸነፍበት አክሽን ፊልም! ልየነቱ በሚሊዮነች የሚቆጠሩ መሪ እና አጃቢ ተዋንያን የሚሳተፉበት መሆኑና ለወራት የሚወራለት መሆኑ ብቻ ነዉ! የሆነዉ ሆኖ አሸናፊዉና አጃቢዎቹ ቀድሞ ዉጤቱ የታወቀበትን ምርጫ የሚባል ድራማ መሰል ነገር ማካሄድ ለምን አስፈለጋቸዉ? ቃለ ተዉኔቱን… ዝግጅቱን… ቀረፃዉን…. ዳኝነቱን አንድ አካል ብቻዉን በተቆጣጠረበት ቲያትር ዉስጥ መግባት የሚያስገኘዉ ትርፍ ይኖረዉ ይሆን? ይመሰለኛል አለዉ…. ባይሆን ኖሮ አጃቢዎቹ ስለምን ይሄን ያህል መፈራገጥ ያስፈለጋቸዉ ነበር? ብዬ እጠይቀለሁ… በርግጥ መልሱን እነሱ ያዉቁታል!  የትወና ብቃትን ለማሳደግ ብቻ የሚያደረጉት ከሆነም ከልብ ያስገርማል …. ይቺ ይቺ በጣም አደገኛ ‘አድቬንቼር’ ነች!  የምሬን ነዉ ያለገባኝ ነገር እንዳለ አላዉቅም ግን ደግሞ እንደዉ አጉል ጉንጭ ከማልፋት… ሰዉም ከማስቸገር ምርጫ የምንለዉ ጉዳይ እዉነተኛ የፉክክር መድረክ እስኪሆን ተወት ብናደርገዉስ? ባይሆን መሰራት ያለባቸዉን መሰረታዊ ጉዳዮችን በርትተን እንስራ….፡፡
የዲሞክራሲ ሂደት?
የሆነዉ ሆነና እቺ ዲሞክራሲ የሚሏት “ዛር” ኢትዮጵያ ዉስጥ ምች ሆን ሞልቶላት የምትቆመዉ? ብትለመን ብትለምን አልወርድ አለች አይደል? ለነገሩ ብቅ ስትል ገና አስደንብረዉ እያባረሯት በየት በኩል ትምጣ? ይልቅዬ ‘ዲሞከራሲዊነት ሂደት ነዉ’ የሚባለዉ ተረት ተረት አብሮን ሊያረጅ ነዉ አይደል? ከምር 10 ዓመት ሆነዉ እኮ….! እናማ መቶ አመት እስኪሞላዉ ልንጠብቅ ነዉ ማለት ነዉ?
በነገራችን ላይ የዚህ ‘ሂደት ነዉ’ የሚሉት ማሳበቢያን ፅንሰ-ሃሳብ ከየት ይሆን ያገኟት ብዬ ሳስብ ድንገት እንግሊዝያዊዉ የኢኮኖሚክስ ሊቅ አዳም ስሚዝ ‘The Wealth of Nations’ የሚለዉ መፃሃፉ ዉስጥ ቶሸንቅሮት ኖሮ አገኘሁትና ‘እነኚ እንግሊዞች ተኮለኞች ናቸዉ….’ የሚሉት ስንኝ ወዲያዉ ትዉስ አለኝ፡፡ ለነገሩ ስሚዝ ስለዲሞክራሲ አስቦ የተናገረዉ ሳይሆን ስለእድገት ሲያወራ ያነሳዉ ሃሳብ ነዉ፡፡ እንደ ሰዉየዉ አባባል የሃገራት የኢኮኖሚ እድገት ተፈጥሮላዊ ሂደቱን ጠብቆ የሚመጣ ዝግመታዊ ለዉጥ (the natural progress of opulence) የሚለዉ አይነት ነዉ፡፡ እንዲህ ማለት ደግሞ ዛሬ የበለፀጉት ሃገራት የደረሱበት የእድገት ደረጃ ላይ ለመድረስ ዕዉደቱ ይተበቅ ከተባለ ለታዳጊ ሃገራት ከመቶ አመት በላይ ሊፈጅ ነዉ፡፡ ሃሳቡን ብዙ ሙሁራን ፉርሽ ያደረጉት ጉዳይ ቢሆንም እኛ ቤት ሲመጣ ታዲያ ዲሞክራሲዊ ለዉጥ በሂደት የሚገኝ ነዉ ከሚባለዉ ማስመሰያ ጋር መሳ ለመሳ የሆነ ይመስላል፡፡ ለምን ቢባል ይሄዉ ሃያ አራት አመታትን አስቆጠርን ያየነዉ መሻሻል የለም … እናም መቶዋን ልነደፍን ነዉ ማለት ነዉ?
ነገሩማ የሚመስለዉ ወደኋላ መመለስ የጀመርን እንጂ ወደፊት መንቀሳቀሱ ሲያምራችሁ ይቀር የተባልን ነዉ፡፡ ወደ ኋላ መንሸራተት እንደ ሃገርና እንደ ስርዓት ትልቅ ኪሳራ ነዉ… ‘የዲሞክራሲ ውርጃ’ አይነት ነገርም ይመስላል፡፡ …. ከምር እንዴት ቁልቁል እንወርዳለን? እዚህ ላይ ፖላንዳዊዉ የምጣኔ ሃብት ሙሁሩ ፖል የተናገረዉን መጥቀስ የተገባ የሆናል…. ‘ሰዉ ከሆንን ምን እንደ ዉሻ ወደ ትፋታችን ይመልሰናል ይልቁንስ የተሻለ ሁኔታን እንፈጥራለን እነጂ’… ያላትን አይነት ሽንቆጣዉን ያስታዉሷል (if we were to emerge alive, we should not return to previous status quo but … form a better world)….. እናማ በዚህ ሁኔታ ከቀጠልን ተስፋችን ምን ይሆን? ይሄ መከረኛ ትወልድ ያሰበዉን ሳይናገር… የፈቀደዉን ሳይመርጥ… አቛሙን እዳሻዉ ሳይገልፅ ዘመናትን ጠብቆ ያሰበዉ ሳይሳካ ሊያለፍ መሆኑ አሳዛኝ ነዉ፡፡
‘እና ምን ይሁን?’ የሚሉ ጠያቂዎች አይጠፉምና ለማለት የተፈለገዉን ማስረዳት ይገባል፡፡ ጉዳዩ እንግዲህ ኢንዲህ ነዉ….. ዲሞክራሲያዊ ሂደቱን የጠበቀ ለዉጥ ለማየት የግድ ዘመናትን በናፍቆት መጠበቅ የለብንም…. ሂደት ነዉ እያሉ መቀለዱን አቁመን ዛሬዉኑ መደረግ ያለበትን ማደረግ የሁሉም ወገን ሃለፊነት መሆኑን መገንዘብ ይገባል፡፡ምርጫ ማካሄድ በራሱ ግብ አይደለም! ይልቁን ዲሞክራሲያዊ ስርዓትን ለመገንባት ከሚጠበቁ  ግብዐቶች መካከል አንዱ ብቻ ነዉ:: ኢትዮጵያ ዉስጥ ለዲሞክራሲያዊ ስርዓትን እንገነባለን የሚባለዉ ለተፈላጊዉ ስርዓት መታጣት ተግዳሮት የሆኑ ነገሮችን ምንነትን ከስር መሰረቱ አጥርቶ ሳይለዩ ከላይ ከላይ በመጋለብ ነዉ:: ዋናዉን የስርዓቱን በሽታ መርምሮ ከለዩ በኌላ መፍትሄ ከመፈለግ ይልቅ የተያዘዉ ምልክቶችን ማስታመምና ግባዐቶች ላይ መረባረብ ነዉ:: እንደ ሚታወቀዉ ሃገሪቱ ሊፈቱ የማይችሉ የሚመስሉ ቅራኔ ዉስጥ ሰምጣ ገብታለች…. ታፍና ከመሞቷ በፊት የነፍስ አድን ስራዎች መሰራት አለባቸዉ፡፡
መድሃኒቱ
ቀዳሚዉና ዋንኛዉ ጉዳይ፡- ለታሪክ ቅራኒዎቻችን መፍትሄ ማበጀቱ ነዉ፡፡ በአንድ ወቅት… በወዲኛዉ ዘመን በበርካታ ቤሔርና ቤሔረሰቦች ላይ የደረሰ በደል አለ ይባላል፡፡ ይህም የመታገያ አጀንዳ ከሆነ ከአራት አስርት ዓመታት አለፉ:: እርግጥ ነዉ ኢትዮጲያ ዉስጥ የሚኖሩ ህዝቦች ሁሉ እከሌ ከከሌ ሰይባል በጭቆና ዉስጥ ነበሩ… (ምናልባት ዛሬም ያ ሁኔታ የተለወጠ አይመስልም)፡፡ እናም በተለየ መንግድ የበደል ገፈት ቀማሽ የነበሩ ቤሔሮች፣ ቛንቛ ተናጋሪዎችና የእምነት ተከታዮች ነበሩ፡፡ የዝሆን ጆሮ ይሰጠኝ አልሰማሁም ወይም አይኔን ግንባር ያደርገዉ አላየሁም ብሎ ሽምጥጥ አድርጎ ለመካድ ካልሆነ በቀር ታሪክ የመዘገባቸዉ እዉነታዎች አሉ::  በሚኖሩበት ስፍራና ቀየ ስንክሳር ያዩ… በማንነታቸዉ እንዲያፍሩና እንዲሸማቀቁ ተደርገዉ የነበሩ የህበረተሰብ አካላት ነበሩ ምናልባተም ዛሬም ቅርፁን ይለወጥ እንጂ በዚህ ሁኔታ ዉስጥ የሚያለፉ ህዝቦች አሉ፡፡ በሌለላ አነጋገር የአማራና የትግራይ ተወላጅ ያለሆኑ እንዲሁም የኦርቶዶክስ ክርስትና ተከታይ ያልነበሩ ህዝቦች ላይ በተለየ መልኩ የደረሰ በደልና ስቃይ ነበር፡፡ የአፄ ሚንሊክ የግዛት ማስፋፋትና ትልቛን ኢትዮጲያን በመፍጠር ሂደት ዉስጥ የፈጠረዉ ጠባሳ ያለተፈቀ ሃቅ ነዉ፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ይህ ሁኔታ ሆን ተብሎ በተፈጠረ የማጋጋያና የማጋነኛ የፈጠራ ንግርቶች ታጅቦ በህዝቦች ማካከል በጋህድ የሚታይ ቅራኔን ፈጥሯል፡፡ በዉጤቱም ግልፅ የሆኑ መናናቆችና መጠላለፎች በሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች በአሁኑ ወቅት እየታዩ ነዉ፡፡ ዛሬ በርካታ አስደንጋጭ  ሁነቶች እየተሰተዋሉ ነዉ …. በፊዉዳሉ ዘመን ለጋብቻ አጥንት ይቆጠር እንደነበረዉ ሁሉ በኛም ዘመን ለሁለት ጥንዶች መጋባት መፈላለጋቸዉና ማፋቀራቸዉ ብቻ በቂ አልሆነም ዘርን ማስተካከልም ተቀዳሚ ጉዳይ ሆኗል ፡፡ ይሄ ደግሞ በከተሞች ጭምር የሚያጋጥም ጉዳይ ነዉ፡፡ በግለሰቦች ደረጃ ያለዉን ማንሳቱ በህዝቦች ማካከል የቱን ያህል ስር የሰደደ የመጠፋፋትና የበቀል ስሜት እያደገ እንደሆነ የሚያመላክት አይነተኛ ሁነት በመሆኑ ነዉ፡፡ ቁምነገሩ ይህን እያወራን እና እያራገብን እስከ መቼ እንዘልቃለን የሚለዉ ነዉ፡፡ እዉነተኛዉ አደጋ አይኑን አፍጥጦና ጥርሱን አግጦ እኪመጣ ከዚያም እኪያጠፋን እተጠባበቅን ያለን ነዉ የምንመስለዉ፡፡ አሳዛኙ ጉዳይ ታድያ ይህ ሁሉ ዐደጋ በዚህና በመጪዉ ትዉልድ ላይ የተደቀነዉ ትዉልዱ በግል ላልፈፀመዉና ላልደረሰበት በደል ነገር ግን ያለፈዉ ትዉልድ ያወረሰዉ ስንክሳር መሆኑ ነዉ፡፡ የዚህን ማለቂያ የሌለዉን የመካሰስ ወጥመድ ሰብሮ መዉጣት የሁሉም ወገን ሃላፊነት መሆን ይኖርበታል:: ለዚህ ደግሞ  ድፍረት ይጠይቃል… እዉነተኛ እርቅና የወገናዊነትን መንፈስ ለመፍጠር ከበዳይም ከተበዳይም ወገን ተወላጅ የሆንን ሁሉ ደፍረን ልንቀበለዉ ጨክነን ልንጋተዉ የሚገባ እዉነታ አለ፡፡
ተወደደም ተጠላ በአንድ ሃገርና አከባቢ እንድንኖር ተፈጠሮ ግድ ብላናለች…ምንም ባንፈላለግ እንኴን ልንነጣጠል አንችልም… ይህ ቀዳሚዉ ሃቅ ነዉ፡፡ ሌላኛዉ ትላነት ለደረሰዉ ጥፋትና በደል የዚህ ትዉልድ ሰዎች ቀጥተኛ ተሰታፊዎች አይደለንም፡፡ ይሄን ታሳቢ አድርግን ቀጣዩን እርምጃ መዉሰድ ተገቢ ይሆናል:: ስለሆነም ለዚህ የዉርስ ፀብ መፍትሔ ማበጀት አለብን፡፡ ሃቁ ይህ ነዉ… አፄ ሚኒሊክና ጦራቸዉ አደዋ ላይ ወራሪዉን ጠላትን አሳፈሮ በመመለስ በሰሩት ገድል የኢትዮጲያ ብቻ ሳይሆኑ የጥቁር ህዝቦች ሁሉ ጀግና እደነበሩት ሁሉ በሌላዉ ገፅታቸዉ ደግሞ ግዛት ለመስፋፋት በደረጉት ዘመቻና በተከቱሉት ፖሊሲ ኢሰባዉነት የተሞሉ ጨፍጫፊ ነበሩ፡፡ በተለይ በአርሲ፣ በባሌ፣ በሐረር፣ በቦረና፣ በወላይታ፣ በከፋና በሌሎችም አከባቢዎች የደረሱ ዘግናኝ ጥፋቶች የማይረሱ የሃያኛዉ ክፍለ-ዘመን የታሪካችን መጥፎ ገፅታ አንዱ አካል ነዉ፡፡ ለዚህ ጥፋት የኦሮሞ ህዝብ እና ሌሎችም ቤሔሮች ብቻ የሚቆጩበት… የአማራ ህዝቦች ብቻ ለዘመናት የሚወቀሱበት ጉዳይ ሊያቆም ይገበዋል፡፡ የድርጊቱ ፈፃማዎች በዚያ ዘመን የነበሩ የስርዓቱ ጠበቂዎች ሲሆኑ በደሉ የደረሰዉ ግን በሁሉም ኢትዮጵያዉያን ላይ እንደሆነ ሊታሰብ ይገባዋል፡፡ ስለሆነም ሚኒሊክ መወገዝ ካለባቸዉ በጋራ እናዉግዝ … ለችግሩ ሰለባ ለሆኑ ሰዎች መታሰቢያ ማድረግ ካለብን በጋራ ስንዘክራቸዉ እንኑር…! ይህን ጉዳይ መቛጨት የሚቻለዉ ሃያት ቅደመ ሃያቶችህ በድለዋል የሚባሉት የአማራ ተወላጆች ሃያት ቅድመ ሃያቶቻችን መከራን ተቀብለዋል ለሚሉ ለሌሎቹ ቢሔሮች ሃዘናችሁ ሃዘናችን ነዉ … ያለፈዉ ትዉልድ ስራ ተገቢ አይደለም ብሎ በደፈናዉ ይቅር በመባባል ብቻ ከሆነ ማድረግ ነዉ፡፡ ተበድለናል የሚሉ ወገኖችም ይቅር ለማለት ዝግጁ መሆን ይኖርባቸዋል:: ይሄ ጉዳይ መፍትሄ ሳይበጅለት ዲሞክራሲያዊ ስርዓት እንገነባለን ብሎ መነሳቱ አለያም ለዉጥ እናመጣለን ማለት የህልም እሩጫ ከመሆን አያልፍም::
ሁለተኛዉ ጉዳይ፡- ከመጀመርያዉ ሃሳብ ጋር የተያያዘና ተቀዋሚ ነን ብለዉ የቆሙ ሃይሎችን ይመለከታል:: ከትዉልድ ትዉልድ የተሸጋገረዉ ተቃርኖ መፍትሄ ሊበጀለት ባለመቻሉና ተያያዥ በሆኑ ጉዳዮች ላይ መስማማት ባለመፈለግ አንድ ኢህዲግን ለመገዳደር ዘጠና ምናምን ፓርቲዎች ተፈጥረዋል:: ብዙዎች ስለምን በሃገር ዉስጥም ሆነ በዉጭ ያሉ የፖለቲካ ሃይሎች የጋራ ተቀናቃኝ የሚሉትን ሃይልን ለመታገል ሲሉ መስማማት እንኳን ይሳናቸዋል የሚለዉ ጥያቄ መልስ የሚያጡበት ጉዳይ ነዉ:: መልሱ ግን ቀላል ግልጽ ነዉ::አንደኛዉ ያለፈዉ ታሪካዊ ተቃርኖ የጋራ ግብ እንዳይኖራቸዉ አድርጔቸዋል…. የጋራ ግብ ቢኖራቸዉ እንኳን ተቀራርበዉ ለመወያየትና ከልብ የሆነ ጥምረትም ይበሉት ጅኒ ቁልቋል ለመፍጠር አልተቻላቸዉም:: ትልቁ የሙግት መከፈቻና የስጋት ምንጭ ሊሆን የሚችለውም እነዚህ ገዢዉን ግንባር እንቃወማለን የሚሉ ሃይሎች እርስ በርስ መቀዋወማቸዉ ብቻ ሳይሆን በጠላትነት ስሜት መተያየታቸዉ ጭምር ነዉ::ስለተመሳሳይ ጉዳይ በተለያየ መድረክ በተመሳሳይ ቌንቌ እየተናገሩ በህብረት ግን መስራት ሲሳናቸዉ ሲታይ የሚገርም ትይንት የሚሆነዉ ያኔ ነዉ::  ሌላኛዉ ጉዳይ ስለመጪ ጊዜ ያላቸዉ አተያይ ጉራማይሌ መሆኑ ነዉ:: አይበለዉና ይህ የከፋዉና የመረረዉ ህዝቡ ነግ በግብታዊነት ተነስቶ ለዉጥ እንፈልጋለን ብሎ በሌሎች ሃገራት እንደታየዉ ስልጣን ላይ ያለዉን ሃይል ቢያባርረዉ ተቃዋሚ ነን የሚሉት ሃገሪቷን በየትኛዉ ፍኖተ ካርታና ፕሮግራም ሊመሯት ይሆን? ይህን የመሰለለዉን ተቃርኖ መፍታት ሳይቻላቸዉ በሰላማዊዉ መድረክም ሆነ በሌላ ዘዴ የስርዓት ለዉጥ እናመጣለን ብለዉ የተነሱ ሃይሎች ሃገሪቱን እና ህዝቡን ወደሌላኛዉ አዙሪት ዉስጥ ያስገቧታል የሚለዉ ስጋትን የምንጋራ ጥቂቶች አይደለንም:: ዋናዉ ጉዳይ ተቃዋሚዎች ላለመስማማት የተስማሙበትን ባህል ቀይረዉ መቀራረብና በጋራ መስራት ካልተቻላቸዉ  ስልጣንን እደንደተመኛት ሳይወርሷት እኛም ዲማክራሲን እንደናፈቅናት ሳናገኛት በምድረ በዳ መቅረታችን የምር ይመስላል::
ሦወስተኛዉ ጉዳይ ከላይ ከተጠቀሱት አበይት ሃሳቦች ጋር በቀጥታ የሚያያዝና መዳረሻ ሊሆን የሚገባዉ ነዉ::ይሄዉም ለዘመናት የተቆለሉ ፖለቲካዊ ቅራኔዎችን በሰከነና በሰለጠነ መንግድ መፍትሄ እዲያገኙ የማደረግ ሂደት ነዉ፡፡ በሌላ አነጋገር ከመቸዉም ጊዜ በበለጠ ስለ ቤሔራዊ እርቅና ስለ ሃገራዊ መግባባት መሰራቱ የተሸለ መሆኑን መረዳት የተገባ ነዉ፡፡ በርግጥ ይህን ሃሳብ ብዙዎች ያዝ ለቀቅ ሲያደርጉት ይስተዋላል፡፡ የሆነዉ ሆኖ ሁሉም መንታ ልብ መሳይ ናቸዉ፡፡ ለምን ቢባል ሲገፉበት አይታይም…. ዛሬ ስለ እርቅ በተናገሩበት አንደበት ነገ ሲያወግዙና ሲፈርጁ ይታያሉ፡፡ እረቀ ሰላምን ለማስፈን ቀዳሚዉ ጉዳይ እዉቅና መስጠትና መከባበር ነዉ፡፡ እዉቅና መስጠት እዉነታን ከመቀበል ይጀምራል፡፡ያለፈን ታሪክ ተቀብለን መፍትሄ እንደምንሻለት ሁሉ የዛሬዉንም ነባራዊ ሁኔታ በቅጡ መረዳት የተገባ ይሆናል:: ተወደደም ተጠላም ባለንበት ዘምንም ሆነ በመጪዎቹ አመታት አሁን ስልጣን ላይ ያለዉ ሃይል ባሻዉና በፈቀደዉ ምንገድ ሃገሪቱን እየመራ የመቀጠሉ ነገር  እዉን ይመስላል፡፡ ይህን ሃይል ያገለለ የእርቅ ሃሳብም ሆነ ሌላ አይነት እንቅስቃሴ መድረሻዉ የትም ነዉ፡፡ ስለሆነም ለማዉገዝና ለማጥላለት የሚያስንፈዉ ሃሳበችን ስልጣን ላይ ያለዉን ሃይል እንደ መንግሰት ተቀብሎ ያስገኛቸዉን ዉስን ነገር ግን ነባራዊና አዉንታዊ ለዉጦች ወይም እድገቶች አክብሮ እዉቅና መስጠት ተቀዳሚዉ እርምጃ ሊሆን ይገባዋል፡፡ የዚህ አይነቱ አቀራረብ ተንበረካኪ.. ተለጣፊ… ሌላለም ሌላም ነገሮችን ሊያስብል እንደሚችል ይገመታል፡፡ ይሁን እንጂ እዉነት ስለሆነ በዚህ መንገድ መጔዙ ግድ ይለናል፡፡ ፈረንጆቹ walk the talk እንደሚሉት የምናወራዉን ልንተገብረዉ ይገባል፡፡ እዚህ ላይ ለማለት የተፈለገዉ ጠላትነትን ብቻ ግብ ያደረገ ዘለቄታ የሌለዉ አካሄድ ስለሚሆን መደረግ ያለበትን ሁሉ አድርጎ እርቅና ድርድር ለመፍጠር የሚቻለባትን በር ክፍት አርጎ ቢያንስ መጠባበቁ የተገባ ነዉ::
እንደ መዉጫ
ከላይ የተዘረዘሩት ቅድመ ሁኔታዎች ባልተሟሉበት ሁኔታ ዲሞክራሲ … መብት… ለዉጥ …ትግል ቢባል እመኑኝ የትም አንደርስም፡፡ ቢሞከር እንኴን ከዚህ ቀደም እደታዩት የታሪክ አጋጣሚዎች ታጥቦ ጭቃ ከመሆን ፈቅ እንደማንል ለመተንበይ ነብይ ሞን አያሻም፡፡ ስልጣን ላይ ያለዉ ሃይል በታዓምር ዲሞክራያዊ ሊሆን እንደማይፈልግ እየታወቀ… ሰልፍ ቢወጣ… ባምርጫ ላይ ምርጫ ቢደረደር እንደዉ አጉል መፈራገጥ ለመላላጥ የሚሉት አይነት ካልሆነ በቀር ጠብ የሚል ነገር ይኖራል ማልት ቂልነት ከመሆን የሚያለፍ ነገር የለዉም፡፡ ዲሞክራሲያዊነት ደግሞ ለድርድር መቅረብ የለለበት የለዉጥ መንገድ መሆን ይኖርበታል፡፡ ሌላ ዙር ጦርነትና ወይም ሌላ ምዕራፍ አብዮት ለሃገሪቱም ሆነ ለህዝቡ የሚበጅ አይሆንም፡፡ ስለሆነም የምንፈልገዉን አይነት ዲሞክራሲያዊ ስርዓት እዉን ለማድረግ የሚቻለዉ የዘመናት የታሪክ ቅራኔዎችን በቅንነት አይቶ መፍትሄ እንዲያገኙ በማድረግ፣ ተቃዋሚዎች እርስ በእርስ ከመቀዋወም ሲዎጡና በመሰረታዊ ጉዳዮች ላይ ተግባብተዉ ለለዉጥ አብረዉ መስራት ሲችሉ ነዉ::የነኝህ ሁለት መሰራታዊ ጉዳዮች እዉን መሆን ወደ ሶስተኛዉ ግብ የሚያንደረድረን ይሆናል:: ይኄዉም ከገዢዉ ሃይል ጋር ለመደራደርና መገባባት ላይ ለመድረስ የሚያስችል አቅም የሚፈጥር ሁነኛ መንገድ ተደርጎ ሊወሰድ ይቻላል:: ያኔ ሁሉንም ወገን ያሳተፈ ስርዓት መመስረት ሲቻል የምንፈልገዉ የሰዎች መብት መከበር፣ ሰላም፣ እኩልነት፣ ነፃነት፣ እድገት ብልፅግና በምንወዳት ሃገራችን እዉን ማድረግ እንችላለን:: ይሁንና ይህን ህልም የሚመስል ምኞት እዉን ለማድረግ ስንት ዘመን ይፈጅብን ይሆን? ተምኔቱን ተጨባጭ ማደረግ የሁሉም ዜጎች ሃላፊነት ሊወሆን ይገበዋል፡፡
ከ ቶፋ ቆርቾ
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!

Thursday, December 11, 2014

በሰላማዊ ተቃዋሚዎች ላይ የደረሰውን ጥቃት እናወግዛለን !!!

በአብዛኛው በወጣት ወንዶችና ሴቶች የተገነባው ሰማያዊ ፓርቲ አባል የሆነበት የዘጠኝ ፓርቲዎች ኅበረት፣ “ነፃነት ለፍትሃዊ ምርጫ” የተሰኘ የአንድ ወር መርሀ ግብር አውጥቶ፤ ችግሮችን ተጋፍጦ አብዛኛውን ተግባራዊ አድርጓል። የመርሀ ግብሩ አቢይ አካል የነበረውና በህዳር 27 እና 28 ሊከናወን ታድቆ የነበረው የ24 ሰዓት የአደባባይ ተቃውሞ ግን በአገዛዙ የኃይል እርምጃ ምክንያት በታቀደው መንገድ ሊከናውን አልቻለም። የህወሓት ቅልብ የሆኑት ሲቪል የለበሱ ሰላዮችና የፌደራል ፓሊስ በተቃውሞው ተሳታፊዎች ላይ ኢሰብዓዊ የሆነ ጥቃት ፈጽመዋል።
ከጅምሩ፣ የፓርቲዎቹ ኅበረት የተቃውሞ ማሳወቂያ ደብዳቤውን ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለማስገባት የገጠመው ችግር የህወሓት አገዛዝ የመንግሥትን መዋቅር ለፓርቲ ሥራ፤ የመንግሥት ተቀጣሪዎችን ደግሞ እንደ ህወሓት አገልጋዮች የሚጠቀምባቸው መሆኑ አንዱ ማሳያ ሆኗል። ሰላማዊ ሰልፍ እንደሚያደርጉ ማሳወቅ የፈለጉት ፓርቲዎች ህወሓት የዘረጋውን አፋኝ ሥርዓት የሚታገሉ በመሆናቸው ብቻ ደብዳቤዓቸውን የሚቀበል እንኳን አጥተው ተጉላልተዋል። ለሰልፉ ቅስቀሳ ማድረግም በራሱ እንደ ወንጀል ተቆጥሮ ወጣቶች ተንገላተዋል፣ ተደብድበዋል፣ ታስረዋል። ያም ሆኖ ውጣ ውረዶች ታልፈው ቅዳሜ ህዳር 27 ቀን 2007 ዓ. ም. ደረሰ።
የኅበረቱ አመራሮች፣ አባላት፣ ደጋፊዎችና ጥሪውን የሰማ ሕዝብ ወደ መስቀል አደባባይ ማምራት ሲጀምር ሲቪል የለበሱ የአገዛዙ ታጣቂዎች እና ፌደራል ፓሊሶች ከሰንደቅ ዓላማዎችና መፈክሮች ባለፈ አንዳች ነገር ያልያዙትን እድሜያቸው ከሃያዎች ያልዘለሉ ውድ የኢትዮጵያ ልጆችን ደብድበዋል፤ ብዙዎቹም አፍነው በአሰቃቂ ሁኔታ እያንገላቱ ወደ እስር ቤቶች ወስደዋል። ወጣቶች ተወልደው ባደጉበት አገር፤ ስሜታቸውን በነፃነት ለመግለጽ በመድፈራቸው ብቻ በጭካኔ ተረግጠዋል፤ ተፈንክተዋል፤ እጅና እግሮቻቸው ተሰብሯል።
ግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ይህ የህወሓትን ፋሺስታዊ እርምጃ አጥብቆ ይቃወማል። ግንቦት 7፣ ህወሓት ከስልጣን እስካልተወገደ ድረስ እንዲህ ዓይነቱን ፋሺስታዊ ተግባር መፈፀሙን የማይተው እኩይ ኃይል እንደሆነ ያውቃል፤ በዚህም ምክንያት የትግላችን ግብ ህወሓትን ማስወገድና በምትኩ የኢትዮጵያ ሕዝብ ይሁንታ ያገኘ መንግሥት መመሥረት መሆን ይኖርበታል ብሎ ያምናል፤ ለዚህም ይታገላል።
ግንቦት 7፣ ህዳር 27 ቀን 2007 ዓ.ም. “መብቶቻችንን በህወሓት ዘረኛ አምባገነኖች አናስነጥቅም” በማለት አደባባይ የወጡ ወጣቶችን ጽናት ያደንቃል። ህወሓት የሚለውን ሳይሆን የይስሙላ ህጉ የፈቀደላቸውን ለማድረግ በመድፈራቸው በህወሓት የህግ ማዕቀፍ ውስጥ ሆኖ የሚደረገውን ትግል አንድ እርምጃ ወደፊት አራምደውታል።
እያንዳንዱ የፓለቲካ ድርጅት ከዚህ ኩነት የሚወስዳቸው ተጨማሪ ትምህርቶች ቢኖሩም የሚከተሉትን ነጥቦች ብዙዎችን ያስማማሉ ብለን እናምናለን።
1. ህወሓት በምንም ዓይነት ቢሆን የያዘውን ስልጣን ለሕዝብ ፈቃድ ማስገዛት አይፈልግም፤
2. ህወሓት አገራችን ወደ ትርምስ እየገፋት እንደሆነ ግልጽ እየሆነ መጥቷል፤
3. ስልጣኑን የሚያሳጣው ከመሰለው እና አቅሙ እስካለው ድረስ ዘግናኝ እርምጃዎችን ከመውሰድ አይመለስም፤
ከህወሓት አገዛዝ መገላገል የሚቻለው ተገዶ ሲወገድ ብቻ ነው። ህወሓት እንዲወገድ ደግሞ የመጨቆኛ አቅሙ መዳከም ይኖርበታል። ህወሓትን የማስወገጃ አማራጭ መንገዶች ብዙ ሲሆኑ ተቀናጅተው ቢሠሩ የበለጠ ውጤታማ ይሆናሉ ብለን እናምናለን፤ “ሁለገብ ትግል” የምንለው የትግል ስልት ጭብጥ ይህ ነው። “እምቢ ለነፃነቴ” ብሎ የተነሳ ሕዝብ ህወሓትን ምን ያህል እንደሚያስደነግጥ በተደጋጋሚ ታይቷል። ህዳር 27ን መንደርደሪያ አድርገን በመውሰድ ከዚህ በተሻለ ለተደራጀ ሕዝባዊ እምቢተኝነትና አመጽ ራሳችን እናዘጋጅ።
በዚህ አጋጣሚ ግንቦት 7፣ ለመከላከያ ሠራዊት እና ፓሊስ አባላት ተደጋጋሚ ጥሪዎችን ማድረግ ይሻል። የመከላከያ ሠራዊት እና ፓሊስ አባላት እንደማንኛውም የኢትዮጵያ ዜጋ በህወሓት ዘረኛና አምባገነን አገዛዝ የተበደላችሁ መሆኑን እናውቃለን። የህወሓት ሹማምንት ከሆኑ አዛዦቻችሁ መላቀቅና ራሳችሁን ነፃ የማውጣት ኃላፊነት የወደቀው በእናንተው በራሳችሁ ላይ ነው። ሠራዊቱ ራሱን በራሱ ነፃ ማውጣት ይኖርበታል። የጊዜ ጉዳይ ካልሆነ በስተቀር ህወሓት መወገዱ የማይቀር በመሆኑ ሠራዊቱ ራሱን ነፃ አውጥቶ ከሕዝብ ጋር ካልወገደ እጣ ፈንታው የተሸነፈ ሠራዊት መሆን ነው። ከዚህ በላይ የሠራዊቱ አባል እየደበደበ ያለው የራሱን ልጅ፣ ወንድሙን ወይም እህቱን እንደሆነ ይወቅ። ይህ ወሳኝ ጊዜ ነው እያንዳንዱ የሠራዊቱ አባል በግል ኃላፊነት ያለበት መሆኑ ሊሰማው ይገባል።

በሁሉም ዓይነት የትግል ዘርፎች የኢትዮጵያ ወጣቶች በስፋት እየተቀላቀሉ መሆኑ ተስፋ ሰጪ ነው። ጊዜው የለውጥ ነው። የተለያዩ ስትራቴጂዎች ተደጋግፈው እንዲሄዱ መደረግ ያለበት ወቅት ላይ ነን። በህዳር 27 ቀን በህወሓት ቅልብ ሰላዮችና የፌደራል ፓሊሶች አማካይነት የደረሰው ጉዳትና የፈሰሰው ደም ለፍትህና ለነፃነት የተከፈለ ዋጋ ነው። ህመማችሁ ህመማችን፤ ትግላችሁ ትግላችን ነው። የተለያዩ መንገዶች ወደ ነፃነት
አደባባይ እያመሩ ነው።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!

አሳዛኙ ብሔራዊ ውርደታችን

ኢትዮጵያ መንግስት አላት ወይ? የአሜሪካ አምባሳደር ለኢትዮጵያ መንግስት በቀይ ባህር ለሞቱት ኢትዮጵያውያን የሃዘን መግለጫ ላኩ።ኢህአዲግ/ወያኔ እስካሁን አንዳች አልተነፈሰም።Statement by Patricia Haslach, U.S. Ambassador to Ethiopia

Patricia Haslach, U.S. Ambassador to Ethiopia
Patricia Haslach, U.S. Ambassador to Ethiopia
በያዝነው ሳምንት መጀመርያ ላይ ዓለም አቀፍ የዜና አውታሮች በየመን የባህር ዳርቻ፣ በቀይ ባህር ውስጥ ከሰባ በላይ የሚሆኑ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች መስመጣቸው መሰማቱ ይታወቃል።ጉዳዩ በሀገር ቤት እና በመላው ዓለም በሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ዘንድ ከፍተኛ ሃዘን አስከትሏል።
ከእዚህ ጋር በተያያዘ የኢትዮጵያውያንን ልብ ያደማው ጉዳይ ደግሞ የኢትዮጵያ መንግስት ይህንን ቢቢሲን ጨምሮ በርካታ የዜና አውታሮች የተቀባበሉትን ጉዳይ ላይ አንዳች የሃዘን መግለጫ አለማሰማቱ ነው።በትናንሽ አደጋ ለሞቱ ለሌላ ሀገር ዜጎች የሃዘን መግለጫ በማውጣት እና በመላክ የሚታወቀው ኢህአዲግ/ወያኔ ለኢትዮጵያውያን ሞት አንዳች አልመተንፈሱ ሌላው የብሔራዊ ውርደታችን መገለጫ ነው።በሳውዲ ጉዳይ መንግስት እንደሌለን አውቀን ነበር።ዘንድሮም በቀይ ባህሩ አደጋ አረጋገጥን።በፌስቡክ ገፃቸው የእየእለቱን ውሎ የሚለጥፉት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም ሰሞኑን ከ 300 ሚልዮን ብር በላይ ወጣበት ስለተባለው በአሶሳ ስለነበረው ብሔር ብሄርሰቦች በዓል ማውሳታቸው ኢትዮጵያ መንግስት አላት ወይ? ብለው ብዙዎች እንዲጠይቁ ማስገደዱ አልቀረም።
ከእዚህ በታች በአዲስ አበባ የአሜሪካ ኤምባሲ ከሰባ በላይ ለሚሆኑት በቀይ ባህር ሕይወታቸው ላለፈው ኢትዮጵያውያን የሃዘን መግለጫ አወጣ።የኢትዮጵያ መንግስት ስለጉዳዩ እስካሁን ድረስ ምንም አላለም።
”ትናንት በየመን የባህር ዳርቻ ቀይ ባህር ውስጥ በሰጠመችው ጀልባ ሕይወታቸው ባለፈው ኢትዮጵያውያን የተሰማኝን ትልቅ ሃዘን ለኢትዮጵያ መንግስት እና ለሟቾች ቤተሰብ እገልፃለሁ።ልባችን ከሟቾች ቤተሰቦች እና ወዳጆች ጋር ሁሉ ነው” በኢትዮያ የአሜሪካ አምባሳደር ወ/ሮ ፓትሪሽያ ሃስላች

Monday, December 8, 2014

ቴዲ አፍሮን ቦሌ ላይ ለምን አገቱት? – ክንፉ አሰፋ (ጋዜጠኛ)

ወደ አውሮፓ የሚያስገባውን ቪዛ እና ትኬት ይዞ ከወዳጆቹ ጋር ጉዞውን ለመጀመር ወደ ቦሌ አለም-ዓቀፍ አውሮፕላን ጣቢያ አቀና። እዚያው እንደደረሰ የተለመደው የፓስፖርትና ትኬት ቁጥጥር ተደረገ። ሁሉም የተሟላ ነበር። ቴዲ ሸኚዎቹን ተሰናብቶ ወደ ውስጥ ገባ። እለተ ሐሙስ፣ ህዳር 28 ቀን 2007 ዓ.ም.።
የአውሮፓው ኮንሰርት በፊንላንድ፣ ሄልሲንኪ ቅዳሜ፤ ህዳር 28 ቀን ይጀምራል። ፊንላንድና አካባቢው ያሉ የቴዲ አድናቂዎች ትኬት ቆርጠው አርቲስቱን በጉጉት እየተጠባበቁት ነው። የቴዲ አፍሮ ማናጀርም አቡጊዳ ባንድን ይዞ ሄልሲንኪ ላይ ለቅዳሜው ስራ በልምምድ ላይ ይገኛል።
ቴዲን ቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ ተሰናብተው የተመለሱ ወዳጆቹ አውሮፓ ደውለው አርቲስቱን ሄልሲንኪ ላይ እንዲቀበሉት ተናግረው ነበር። ነገሩ እነሱ እንዳሰቡት ግን አልነበረም። ዘግየት ብሎ ሌላ ነገር መጣ። ሰዎቹ ቦሌ ላይ አገቱት። በውድቅት ሌሊት ፓስፖርቱን ነጥቀው ወደ ቤቱ አሰናበቱትም። ይህንን ያደረጉበትን ምክንያትም አልነገሩትም። አስቀድመው ገና ከበሩ ላይ መከልከል ይችሉ ነበር።… ግን ማንገላታት ነበረባቸው። ስሜቱን ለመጉዳት መሞከር ነበረባቸው። ጉልበት እንዳላቸው ማሳየት ነበረባቸው። ፈላጭ፤ ቆራጭ መሆናቸውን ማሳወቅ ነበረባቸው። ቂመኞችና ተበቃዮችም መሆናቸውን መናገር ነበረባቸው። ….
ነገሩ ያልተጠበቀ ባይሆንም፤ ለቴዲ ጠበቆች ግራ ማጋባቱ አልቀረም። በነጋታው ጠበቆቹ ጉዳዩን ለማጣራት ወደ ፍርድ ቤት መሄድ ነበረባቸው። ከፍርድ ቤት ያገኙት ምላሽ በቴዲ አፍሮ ላይ ምንም አይነት የማገጃ ትዕዛዝ ያለመኖሩን ነው። ከዚያም ወደ ኢሚግሬሽን ጉምሩክ እና ሌሎች ጉዳዩን የሚመለከቱ ቢሮዎች ሁሉ አመሩ። እዚያም የጉዞ ማገጃ አልተገኘም። ታዲያ ማን ይሆን ያዘዘው? የካዛንችዙ ስውር መንግስት ስራውን እንደገና ጀምሮ ይሆን?
ጉዳዩ ግራ ያጋባል። እርግጥ ነው። የዛሬይቱ ኢትዮጵያ አንድ ተራ ካድሬ እንዲህ አይነት ተራ ወንጀል የሚፈጽምባት ሃገር ሆናለች። አንዳንድ ቦታዎች ላይ “መንግስት የለም እንዴ?” የሚያስብሉ ወንጀሎች እንደሚፈጽሙ ይሰማል። የቀድሞው የኮሚኒኬሽን ሚንስትር ዴዔታ የነበረው ኤርምያስ ለገሰ፤ በቅርቡ ባሳተመው “የመለስ ትሩፋቶች” የተሰኘ መጽሃፉ አዲስ አበባን ባለቤት አልባ ከተማ ብሏታል።
በልማታዊ አርቲስቶች እለት-ተለት የሚወደሰው ጸሃዩ መንግስት፤ ለልማት የተጋው መንግስት፣ ጭቆናን ያቆመው መንግስት፤ ለዜጎች መብትና ነጻነት የቆመ መንግስት፣ ሃገሪቱን ወደ እድገት እና ትራንስፎርሜሽን ጎዳና ላይ ያስኬደ መንግስት፣ የመቻቻል ባህልን ያመጣ መንግስት…. እንዴት ሆኖ የጥላቻ፣ የቂም እና የበቀል እርምጃ ሊወስድ ቻለ?
ልማታዊ አርቲስቶቻችን ይቅርታ አድርጉልኝና የአስተሳሰብና የአመለካከት ለውጥ ሳይኖር ቁሳዊ ለውጥ ይመጣል ብሎ የነገራችሁ ማን ይሆን? አመለካከታችን ካላደገ፣ እድገት ይታሰብ ይሆን?
ወደ ጉዳዩ ስንመለስ፣ ከፊንላንድ በኋላ ሌሎች ስድስት የአውሮፓ ከተሞች ላይ ኮንሰርቶች ተዘጋጅተዋል። ፕሮሞተሮች ለመሰናዶው ብዙ ወጪ አውጥተዋል። የአርቲስቱ አድናቂዎችም አስቀድመው ትኬት ቆርጠዋል። ይህንን ካድሬዎቹ ጠንቅቀው ስለሚያውቁ ሁሉንም ማጉላላቱ፤ ከተቻለም ማደናቀፉ ደስታን ይሰጣቸዋል። እንዲህ አይነት የድፍረት ስሜት የሚመነጨው አርቲስቱን ሳይሆን ይልቁንም ሕዝብን በጅምላ ከማናቅ ነው። ሕዝብን ከመጥላት። እየገዙት ያሉትን ህዝብ መናቅና መጥላት የት ድረስ ሊያደርሳቸው እንደሚችል የምናየው ይሆናል። እንደ ሰብአዊ ፍጡር ሳይሆን እንደ እንስሳ የሚያስቡ እነዚህ የዘመናችን ጉዶች ሕዝብ የሚወደውን ነገር በሙሉ በመጥላት፤ የህዝብ አካል እንዳልሆኑ እይረጋገጡልን ነው። ከጫካ ከወጡ 21 አመታትን አስቆጥረዋል። አካላቸው ከጫካ ወጣ እንጂ አመለካከታቸው ግን እዛው እንደሆነ ድርጊታቸው ይነግረናል። ከሁለት ዓስርተ-ዓመት በኋላም ጥንት ከሚያስቡበት ከጫካው ህግ አልተላቀቁም።
ይህንን ትልቅ ሃገር እና ይህንን ትልቅ ሕዝብ እየመሩ ለምን እንደመንገስት ሊያስቡ እንደማይችሉ አይገባኝም። መንግስት ሆነው እንደግለሰብ ቂም ይይዛሉ። ቂም ይዘው እንደ ክፉ ሰው ይበቀላሉ። ሀገር ደግሞ በጥበብ እና በማስተዋል እንጂ፤ ከቶውንም በቂም እና በበቀል አትመራም። ይህንን የሚያደርጉ ሁሉ መጨረሻቸው ውድቀት፤ አወዳደቃቸውም የውርደት እንደሆነ ለደቂቃ አስተውለውት የሚያውቁ አይመስለኝም።
እንግዲህ ይህ ተራ ወንጀል በዚህ ድንቅ አርቲስት ላይ ሲፈጸም የመጀመርያ አይደለም። ከወራት በፊትም ወደ አሜሪካ ሊጓዝ ሲል የአየር መንገዱ ካድሬዎች ይዘው ብዙ አጉላልተውት ነበር። እርግጥ ነው ቴዲ አፍሮ ላይ ጥርሳቸውን ነክሰውበታል። ኤርምያስ ለገሰ፤ በ”መለስ ትሩፋቶች” መጽሃፉ ላይ የቴዲን ጉዳይ አንስቶ የገዢው ፓርቲ ሰዎች ይህንን አርቲስት እንዴት በክፉ አይን እንደሚመለከቱት ዳስሷል። ይህ አርቲስት ምናልባት በአንዲት ዜማ ተችቷቸው ይሆናል። እነሱም አላለፉትም። በፍትህ ስም የበቀል ዱላቸውን አሳርፈውበታል። ወህኒ ወርዷል። እስኪበቃቸውም ቀጥተውታል።
ቴዲ አፍሮ ግን ቂም አልቋጠረባቸውም። አሁንም የሚያቀነቅነው ስለ ፍቅር ነው። አሁንም የሚለው እንዲህ ነው። “ፍቅር ያሸንፋል!”
እነዚህ ሰዎች ሃያ ሁለት አመታት ሙሉ ከጥፋት አለመማራቸው ብቻ አይደለም የሚደንቀው። በአንድ ግለሰብ ምክንያት ከሚሊዮኖች ጋር እንደሚላተሙ አለማሰተዋላቸውም የሚገርም ነው። ለሟቹ ፓትሪያርክ ሲሉ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ኦርቶዶክስ ምዕመናን ጋር ተቃርነው ነበር። አንድ የሙስሊም መጅሊስ መሪን ለመያዝ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሙስሊም ምዕመናን ጋር ጠፋጥተዋል።
ዛሬ አንድ ቴዲን ቢያንገላትቱት፣ ቢያግቱትም ሆነ ፓስፖርቱን ቢነጥቁት ለግዜውም ቢሆን የአድናቂዎቹን ስሜት ሊጎዱት ይችሉ ይሆናል። ይህ ድርጊታቸው ቴዲ አፍሮን ቅንጣት ያህል አይጎዳውም። ይልቁንም የበለጠ ተወዳጅ እና የበለጠ ጀግና ያደርገዋል። ከዚህ የፖለቲካ ንግድ እነሱ የሚያተርፉት ነገር ቢኖር የህዝብ ጥላቻን ነው። የቴዲን መታገት የሰሙ የገዢው ፓርቲ ደጋፊዎች ሳይቀሩ እንዲህ ሲሉ ተደመጡ፤ “አሁንስ አበዙት… ሃገራችንን እንድንጠላ አደረጉን….” ካድሬዎቹ ማህበራዊ ድረ-ገጾችን ቢጎበኙ የህዝቡን ስሜት ያነብቡ ነበር።
በሕዝብ አመኔታ ሳይሆን ይልቁንም በጆሮ ጠቢዎችና በመሳርያ በመተማመን እስካሁን ስልጣን ላይ ላላችሁት ገዢዎች ግን አንድ የምለው አለኝ። የፈረንሳዩ አንባገነን ናፖሊዮን ቦናፓርት የነበረውን ሰራዊት እስተውሉ። ይህ ግዙፍ እና የሰለጠነ ሰራዊት በህዝብ እንደ አሸዋ ተበተነ። የግብጹ ሆስኒ ሙባረክ ያልታሰበ እና ያልታለመ ውድቀት የመጣው እንዲሁ በመሳርያ ከመተማመን እና ህዝብን ከመናቅ ነበር። ይህ አስደንጋጭ ትዕይንት ለእናንተ ትምህርት ካልሰጣቸሁ የሱ እጣ ፈንታ ይጠብቃችኋል። መቶ አመት የቆየ አንባገነን ገዢ በታሪክ አላየንም።
zehabesh

Saturday, December 6, 2014

Ethiopia: Senior Blue Party leaders, members and supports have been detained

On Saturday, December 6,2014, the ethnic based Ethiopian government security forces have arrested leaders of Blue and other Party leaders,
 members and supporters at the start of a peaceful public rally to demand free and fair election. Blue Party Chairman Eng. Yilkal Getnet along with senior party members have been detained. This protest rally was organized by a coalition of opposition political parties fully in compliance with the law.
This is a clear manifestation of the governing party’s total dictatorship and absolute intolerance for peaceful decent
At this point, the exact number of detainees is not available nor where they have been detained. We will release more information soon.

‹‹የከተማ ጦርነት አውጃችኋል!የተዘጋጀ ኃይል አለን ልካችሁን ያሳያችኋል›› ኮሎኔል ዘውዴ የየካ/ክ/ከ/ፖ/መ/ኃ

December 6, 2014
ሳሙኤል አበበ (በፖሊስ ታግቶ የነበረ)

ትናንት ከቀኑ 10 ሰአት አካባቢ ልክ እንደ ሰሞኑ ሌሎች ጓዶቻችን ላይ ይደረግ እንደነበረው የፖሊስና የደህንነት አፈና ሁሉ ፍቅረማርያም አስማማውን የህወሓት ቅልብ ደህንነትና ፖሊሶች አፍነው ወሰዱት፡፡ እኛም ቢያንስ ያለበትን ቦታ ለማወቅ ከትንታጉ ጋዜጠኛ በላይ ማናዬ ጋር በመሆን ፖሊስ ጣቢያዎችን ማሰስ ጀመርን፡፡ የመጀመሪያ መዳረሻ የሆነን የየካ ክ/ከተማ አድዋ ድልድይ ፖሊስ ጣቢያ ሆነ፡፡ እንደደረስንም በር ላይ የነበሩትን ሁለት ፖሊሶች ጓደኛችን በፖሊስ ተይዞ ወዳልታወቀ ቦታ ስለተወሰደ እዚህ መኖሩን ለማረጋገጥ ነው ስንላቸው ‹‹ልጁ እዚህ ገብቷል፡፡ ግን ምርመራ ላይ በመሆኑ ትንሽ ቆይታችሁ ኑ!›› ተባልን፡፡

እኛም ‹‹ምን አልባት ሊያድር ስለሚችል እራት እናስገባለት›› አልናቸው፡፡ አሁን እኛን አላናገረንም፡፡ በቀጥታ ውስጥ የቆሙት ሁለት ፖሊሶች ጋር ሄዶ አነጋገራቸውና ተመለሰ፡፡ ‹‹አሁን አይቻልም፡፡ ሂዱና ቆይታችሁ ተመለሱ፡፡›› የሚል ትዕዛዝም ሰጠን፡፡ በትዕዛዙ መሰረት ፊታችንን ከማዞራች ሰከንድ እንኳ ሳይሞላ ከውስጥ በጎርናና ድምጽ ‹‹ኑ ተመለሱ! እናንተም ትፈለጋላችሁ፡፡›› በማለት አምባረቀብን፡፡ እኛም ሳናቅማማ ገባን፡፡ ሁለቱም ፊታቸው ላይ ከፍተኛ ጥላቻና ንቀት ይነበብባቸዋል፡፡ የማስፈራሪያና ማሸማቀቂያ ቃላትን በተደጋጋሚ ይናገራሉ፡፡

እኛ ደገሞ ውስጣችን ያለው እውነት ነውና እንዳሰቡት ልንደናገጥላቸው አልቻልንም፡፡ ጓደኛዬ በላይ ማናዬን ‹‹ስትገባ ስቀሃልና ምን እንዳሳቀህ ንገረን!›› አለው አንደኛው ፖሊስ! በላይም ‹‹ይህ የአኔ የግል ጉዳይ ነውና ልትጠይቀኝም፣ ልነግርህም አልችልም›› ብሎ በልበ­ሙሉነት መለሰለት፡፡ ቀጥሎም‹‹ተፈተሹ!›› ተባልን፡፡ እኛም ‹‹ፍ/ቤት ትዕዛዝ ካልተሰጠ በስተቀር ምንም ሰው ሊፈተሸ አይገባምና እኛም አንፈተሸም›› አልን፡፡ እነሱም አስገድደው ፈተሹን! እንዲያውም ‹‹እኛምኮ ህግ እናውቃለን፡፡ እንድፈትሽም የለበስነው የፖሊስ ልብስ መብት ሰጥቶናል፡፡.ወዘተ..›› በማለት ህጉን ሳይሆን ፍላጎታቸውን ነገሩን፡፡

በዚህም ንትርክ መሃል የክፍለ ከተማው ኃላፊ ኮሎኔል ዘውዴ የተባሉ ሰው ግቢውን ዘልቀው እኛ ጋር ደረሱ፡፡ እንደደረሱም ‹‹እነኚህን ልጆች አውቃቸዋለሁ፡፡ ከአንተ ጋር በተደጋጋሚ ቁጭ ብለን አውርተናል፡፡ ግን ሁሌም ያው ናችሁ፡፡ ሊገባችሁ አልቻለም፡፡›› አሉን፡፡ በእርግጥ እኚህ ሰውዬ ጋር ለሚያዚያ 19/06 ዓ.ም የተደረገው ሰላማዊ ሰልፍ ቅስቀሳ የወጡትን የፓርቲውን አባላት ከመንገድ ለቅመው ያሰሯቸውን ልጆች ለመጠየቅ በሄድኩ ጊዜ ከሁለት ሰዓት በላይ የፈጀ እልህ አስጨራሽ ክርክር አይሉት ውይይት ብቻ ቅጥ የሌለው ንግግር እንዳደረግን አስታውሳለሁ፡፡ ያኔ ያሉኝ ‹‹እናንተ ምን ፈልጋችሁ ነው? ልማቱ ተፋጥኗል፡፡ መንገዱ ኮንዶሚኒየሙ፣ ግድቡ፣ ዩኒቨርሲቲዎች ወዘተ ተገንብተዋል›› በማለት የተሞሉትን ዘከዘኩልኝ፡፡
እኔም ባይሰሙኝም ‹‹እዚህ አገር ያለው ስርዓት የኢኮኖሚ፣ የፖለቲካ እና የማህበራዊ ቀውስ መውጣት ወደማንችልበት አዘቅት ውስጥ እየከተተን እንደሆነ ስነግራቸው etv እንደሚለው ጸረ­ልማት ብለው ከመፈረጅ አልተቆጠቡም፡፡ ዛሬም ከ8 ወር በኋላ ስንገናኝ በአቋማቸው ጸንተው እንዲያውም ከሬድዋን ሁሴን በልጠው አገኘኋቸው፡፡ ከላይ እስከታች እየገላመጡ ‹‹ከእናንተ ጋር እንተዋወቃለን፡፡ የከተማ ጦርነት አውጃችኋል፡፡ ይህ ደግሞ አይቻልም፡፡ ጫካ ግቡና ጦርነት ክፈቱ፡፡ ያኔ የተዘጋጀ ኃይል አለን፡፡ ልካችሁን ያሳያችኋል፡፡›› በማለት የህወሓት/ኢህአዴግን ፍላጎት ነገሩን፡፡ እነሱም እንዳሰቡት ልንሸማቀቅና ልንሰግድላቸው አልቻልንም፡፡ ረዥም ጊዜ ካቆዩን በኋላ ተጠራን፡፡ ስልካችንና መታወቂያችን መንግስቱ የተባለ መጀመሪያ ያገተን ፖሊሲ ይዞት መጣ፡፡ በማዝተዛዘንም ‹‹የያዝናችሁ በአመለካከታችሁ ወይንም እኛ ለአንድ ወገን በመቆም አይደለም፡፡ የያዝናችሁ ለሁላችንም ደህንነት ስንል ነው፡፡ ግን ላንግባባ እንችላለን፡፡›› በማለት አስረዳን፡፡ እኛም መጀመሪያ ዱላ ቀረሽ ንግግር፣ ክብር የሚነኩ ቃላትን ሲተፋ የነበረ ሰው አሁን ይህን ቢለን እንዴትስ ሊገባን ይችላል? ግቢውንም በእኩለ­ሌሊት ለቀን ወጣን፡፡ በመጨረሻም እንዲህ ልላቸው ወደድኩ፤ በእያንዳንዷ ቀን የምትፈጽሙብን ግፍ ለእኛ ብርታት፣ ትግላችንም አስፈላጊ መሆኑን የበለጠ ያስረዳናል እንጅ እናንተ እንደምታስቡት ይህ ግፍ መቀጣጫ ሆኖን ወደየ ቤታችን ፈጽሞ ልንመለስ አንችልም፡፡ ትግላችን እስከ መስዋዕትነት ደረስ ነው!!

Tuesday, December 2, 2014

ለሀገር ነጻነት የወጣቱ ተሳትፎ ቀጣይነት ይኑረው!

 
ከ1997 ምርጫ ማግስት ጀምሮ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ወጣቶችና በሁሉም የእድሜ ክልል የሚገኙ ዜጎች ለሀገራቸው የዲሞክራሲ መብት መከበር እያደረጉት ያለው አስተዋጽኦ ላቅ እያለ መምጣቱ የቅርብ ጊዜ ትውስታ ነው። ይህን ተከትሎ ዛሬ ወጣቱ የወላጆቻችን ደምጽ ይከበር፣ ኢትዮጵያዊነት በዘረኝነት አይፈተንም! ነጻነት ዳቦ አይደለም! እስራትና ግድያ በኢትዮጵያ ይቁም! የወያኔ አገዛዝ በቃን! በሚሉ በበርካታ ወጣቶች ጩኸት የወያኔ ሹማምንትና አገልጋዮቹ ላይ የፈጠረው ድንጋጤ ወጣቱን ሽብርተኛ አስደርጎታል።
ወጣቶች ህዝብን አስተባብረው ለተቃውሞ በማሳደም የወያኔን ዘረኝነት በመቃወም ረገድ የተለያዩ ዘዴዎችን ከሌሎች የነጻነት አቢዎት እንቅስቃሴ በመማር እምቢተኝነትን በማሳየት ጅማሮ ላይ ናቸው። ሰሞኑን በባህርዳር ከተማ የተጀመረው የእምቢተኝነት ዘመቻ በሚቀጥለው በሁሉም የሀገሪቱ ክፍል ይቀጣጠል ዘንድ ወጣቱ ሃላፊነት አለበት። ሀገራችን መስቀለኛ መንገድ ላይ ነች። ሁሉም የማህበረሰብ ክፍል ወያኔን ለማስወገድ በሚደረገው መራራ ትግል ውስጥ የበኩሉን አስተዋጽኦ ማድረግ ይኖርበታል። አባቶቻችን የውጪ ሀገራትን ወራሪዎች ወራራ ለመመከት ሁሉም ሰው የሚችለውን ሁሉ እንዲያደርግ ያደረጉት ጥሪ አሁንም ላይ ይሰራል።
ለራሳችን ክብር፣ አንድነት፣ ለሀገር ነጻነትና ህልውና መከበር ኢትዮጵያዊ እምቢተኝነት የሚጀምረው ከትንሽ ነው። ህወሃት በጠላትነት የፈረጃችሁ የዛሬ ወጣቶች የሆናችሁ ዘመን በሚፈቅድላችሁ ቴክኖሎጂ በመጠቀም በመላው ሀገሪቱ ወረቀት ከመበትን አንስቶ ሌሎች ይትግል ስልቶችን ተጠቀሙ። ኢትዮጵያ ሀገራችሁ በአንድ ጠባብ ዘረኛ ቡድን መዳፍ ውስጥ ማልቀስ ከጀመረች ሰነባብታለች። ዜጎቿ የግለሰብም ሆነ የቡድን መብታቸው ተረግጦ በባርነት እየተገዙ ነው። ጉልበታቸውና ሀብታቸው እየተመዘበረ ሲሆን፤ ለነጻነት፣ ለዲምክራሲና ለፍትህ የጮኹ ሁሉ ሽብርተኛ ተብለው ወደ ማጎሪያ እየተወረወሩ ነው።
ስለዚህ ስለ ሀገራችን፣ ስለራሳችን የግልም ሆነ የቡድን ጥቅም ስንል በሀገሪቱ የትኛውም ከፍል የተጀመረውን የእምቢ አልገዛም ባይነት እንቅስቃሴ እንደግፍ፣ እንሳተፍ! በባህርዳር የተጀመረውን የወጣቶች እንቅስቃሴን አድንቀን ይህ ተነሳሽነት በሌላውም የሀገሪቱ ክፍል መቀጠል ያለበት ነው።
ይህን በማድረግ ወደ ትግሉ በመቀላቀል ካልተሳተፍን በስተቀር ትግላችን አንድ እርምጃ ወደፊት ፈቀቅ ማድረግ እንደማንችል ግንቦት 7 ያምናል። ስለሆነም ሁሉም አካላት በያለበት በየሚኖርበት፣ በሚችለው አቅሙ ሁሉ ወደትግሉ በንቃት ተሳተፍ! አብረን ታግለን ነጻነታችንን እናረጋግጥ! ለኢትዮጵያ ትንሳኤ፣ የነጻነት አዋጆች ነጋሪ፣ አብሳሪ ትውልዶች እንሆን ዘንድ ሳንታክት እንታገል ዘንድ ወቅቱ የሚጠይቀው ጥሪ ነው።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ

Monday, December 1, 2014

ህጋዊ ተቃዋሚዎችን በአክራሪነት ሰበብ ለመምታት የሚያስችሉ ሃሳቦች ቀረቡ

ኀዳር ፳፪(ሃያ ሁለትቀን ፳፻፯ / ኢሳት ዜና :-በሃገሪቱ ህገ መንግስት አንቀጽ 31 መሰረት በህጋዊ መልኩ ተመዝግበው ሰላማዊ የፖለቲካ እንቃስቃሴ የሚያደርጉ ተቀናቃኝ ፓርቲዎችን በሽብርተኝነት እና ጽንፈኝነት በመፈረጅ የጥቃት ኢላማ ለማድረግ መታሰቡን ኢሳት የፌደራል መንግስት የጸጥታ ጉዳዮች ሰሞኑን ከመንግስት ባለስልጣናት ጋር  ካካሄደው ውይይት ለመረዳት ተችሎአል፡፡

የትግራይ፣ቤንሻንጉል ጉሙዝና አማራ ክልል ሃላፊዎች ሰማያዊ ፣አንድነትና መኢአድ ፓርቲዎች ጽንፈኞች በመሆናቸው በአክራሪነት ሲሳተፉ የነበሩ ወጣቶችን በማሰባሰብ ለሽብር እያዘጋጁ ነው በማለት የገዢውን መንግስት ፖሊሲዎች በሰላማዊ መንገድ የሚቃዎሙትን ፓርቲዎችን በወንጀለኛነት ሲፈርጁ ተደምጠዋል፡፡
መልካም ተሞክሮ ነው በማለት በየክልሉ አስተዳደርና ጸጥታ ጉዳዮች ኃላፊዎች የቀረበው ሪፖርትና የወደፊት እንቅስቃሴ በመጭው ምርጫ 2007 የተፈረጁት ፓርቲዎች የህዝብ ድምጽ በማግኘት የገዢው መንግስት ስጋት እንዳይሆኑ ከማሰብ የተነሳ መሆኑን የውስጥ ምንጮች ለኢሳት ገልጸዋል፡፡
በሃገሪቱ በትጋት ከሚንቀሳቀሱና የህዝብ ድጋፍ በብዛት እያገኙ ከመጡት የተቀናቃኝ ፓርቲዎች መካከል የሚመደበው የሰማያዊ ፓርቲን እንቅስቃሴ ለማስቆም እና የምርጫ 2007 ስጋት መሆናቸውን ለማክተም ገዢው መንግስት በየአካባቢው የሚከሰቱ ሃይማኖታዊ እንቅስቃሴዎችን በሙሉ ከተቀናቃኝ ፓርቲዎች ጋር ማገናኘት መጀመሩ ሆን ተብሎ ሰላማዊ ተቃዋሚዎችን ለመምታት የተዘጋጀ መሆኑን ምንጮች ጠቅሰዋል።
የአማራ ክልል አስተዳደርና ጸጥታ ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ አቶ ደሴ አሰሜ  “በክልሉ አክራሪነት አሁን ያለበት ደረጃ ሲገመገም አሁንም ስራ የሚጠይቅ ነገር እንዳለ ተገንዝበናል፡፡ አሁን አሸንፈናል ሙሉ በሙሉ አስወግደናል ብለን አንወስድም፡፡” በማለት አክራሪነት   መልኩን እየቀየረ መምጣቱን ተናግረዋል፡፡
“በተለይ በደቡብ ወሎ ቃሎ አካባቢ የሚገኙ የሰማያዊ ፓርቲ ፣አንድነትና መኢአድ የተባሉት ጽንፈኛ ተቀናቃኝ የፖለቲካ ድርጅቶች የሚያካሂዱት የአባላት ምልመላ ከምርጫ ጋር በማገናኘት በጽንፈኝነት አስተሳሰብ እየተጓዙ በመሆኑ በዚህ ረገድ ከፍተኛ ጥንቃቄ አድርገን መጓዝ አለብን፡፡” በማለት የተቀናቃኝ ፓርቲዎችን ለማሸማቀቅ የሚያስችል እንቅስቃሴ እንዲጀመር ሃሳብ አቅርበዋል።
የቤንሻንጉል ጉሙዝ አስተዳደርና ጸጥታ ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊም  የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ይፈቱ ብለው ያቀረቡትና በሚዲያ ቅስቀሳ ሲያደርጉ የነበሩ አባሎች የአክራሪነትና ጽንፈኝነት አስተሳሰብ የያዙ ናቸው በማለት ለተሰብሳቢው ገልጸዋል፡፡
በአማራ በቤንሻንጉልና በትግራይ የታየው ተሞክሮ በሌሎች ክልሎችና ልዩ ልዩ አስተዳደሮች ተጠናክሮ ሊተገበር እንደሚገባም በስብሰባው ላይ ሃሳብ ተሰጥቷል፡፡
ፓርቲዎቹ እስካሁን ድረስ ህዝቡን ለማደራጀት አቅም ባለመፈጥራቸው አስፈሪ አለመሆናቸውን የገለጹት አንድ ባለስልጣን፣ በሂደት ሃቅም እያጎለበቱ መሄዳቸው ስለማይቀር እስከሁን እንደተወሰደው ያለ ኢርምጃ መውሰድ አስፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል።
ኢሳት የፌደራል መንግስት የጸጥታ ሃይሎች ያደረጉትን ስብሰባ በተመለከተ ተጨማሪ ዘገባዎችን ሰሞኑን ያቀርባል።

Is H&M Turning a Blind Eye to Land Grabs in Ethiopia? A TV4 Investigation

https://www.youtube.com/watch?v=5-ImoKhymL4
http://ecadforum.com/ethiopianvideo/2014/11/30/tv4-exposed-al-amoudi-and-hm/

Thursday, November 13, 2014

ወያኔ/ኢሕአድግ እና ምርጫ 2007

November.11.2014
በያዝነው 2007 ዓ.ም በግንቦት ወር ለሚካሄደው አገራዊ ምርጫ በገዢው ፓርቲ እንዲሁም በተቃዋሚ ፓርቲዎች ቅድመ ዝግጅቶች እየተደረጉ ሲሆን ምርጫ ቦርድም ምርጫውን በበላይነት ለመምራት ቁሳዊና ቴክኒካል ዝግጅቶችን እያደረገ መሆኑን ከገዢው ፓርቲ ልሳን ከሆነው EBC በተደጋጋሚ እየተሰማ ነው፡፡ ይህን ተከትሎ እንደ ከዚህ ቀደሙ ሁሉ በተቃዋሚ ፓርቲዎች መካከል መከፋፈሎች እንዲሁም አለመረጋጋቶች እየተስተዋሉ ሲሆን ለዚህም ምክንያቶቹን በእርግጠኝነት መግለጽ አዳጋች ቢሆንም ካለፉት የምርጫ ተሞክሮዎች በመነሳት የገዢው ፓርቲ ረጃጅም እጆች እንዳለበት መተንበይ አዳጋች አይሆንም፡፡
በዚህ በያዝነው አመት የሚካሄደውን አገራዊ ምርጫን ለመተንበይ በቅድሚያ ከዚህ ቀደም የተካሄዱትን አገራዊ ምርጫዎች በወፍ በረር ቅኝት ማየቱ የግምቱን ይዘት ጠንካራ ያደርገዋል፡፡ በዚህ ጽሁፍ አዘጋጅ እምነት እንዲሁም በተለያዩ ጊዜያቶች ከሚወጡ ጥናታዊ ጽሁፎች ለመረዳት እንደሚቻለው በአገራችን ተስፋ ሰጪ ዴሞክራሲያዊ ምርጫ ተካሂዷል ተብሎ የሚታሰበው በ1997ዓ.ም በተካሄደው አገራዊ ምርጫ ነው፡፡ ለዚህም በርካታ ምክንያቶች ቢኖሩትም በዋነኛነት ገዢው ፓርቲ በወቅቱ ለነበሩት ተቃዋሚ ፓርቲዎች የነበረው ዝቅተኛ አመለካከት (በወቅቱ ቅንጅት የምርጫው ምዝገባ ሊጠናቀቅ ጥቂት ጊዜያት በቀሩበት ወቅት ቅንጅት መፍጠሩን ልብ ይለዋል) እንዲሁም የምዕራባዊያኑን ቀልብ በመሳብ አገሪቷ ለዴሞክራሲያዊ ግንባታ እየተጋች መሆኗን ለማሳየትና ከፍተኛ ፖለቲካዊ ትርፍ ለማግኘት ሲሆን ከዚሁ ጋር ተያይዞም በወቅቱ በመንግስት ይዞታ ስር የነበሩትን የንግድ ተቋማት ወደ ግል ይዞታነት በማዞር (privatization) መንግስት ቀደም ሲል ይተችበት የነበረውን ሶሻሊስምን ወደ ጎን በመተው ዘመኑን መምሰሉን በማሳየት ምዕራባዊያንን ለማሳመን የሚተጋበት ወቅት ስለነበረም ጭምር ነው፡፡ ስለሆነም ያለፉትን የምርጫ ሂደቶችን ለመገምገም ምርጫ 97 እንደመነሻ (base year) በመውሰድ ገዢው ፓርቲ እንዲሁም ተቃዋሚ ፓርቲዎች በምርጫው ላይ የነበራቸውን ሚና በሚከተለው መልኩ ለመዳሰስ ወደድኩኝ፡
ምርጫ 97
ኢሕአድግ 1997ቱ ምርጫ ከላይ ለመጥቀስ እንደተሞከረው ለተቃዋሚዎች በነበረው ዝቅተኛ ግምት ፤ ምርጫውን በበላይነት አሸንፋለው ከሚል የተሳሳተ ግምት እንዲሁም የምዕራባዊያኑን ቀልብ ለመግዛት የዲሞክራሲ በሩን ገርበብ አድርጎ በመክፈቱና ለምርጫው ቅስቀሳ ከዛ በፊት ይሰጡ ከነበሩት የመከራከሪያ ሰዓት በአንጻራዊነት ሰፊ ጊዜ ለተቃዋሚዮች በመስጠቱ ህዝቡ የሁሉንም ፓርቲዎች ፕሮግራም የሚሰማበት እድል ፈጥሯል፡፡ በወቅቱ ከተቃዋሚ ፓርቲዎች አንጻር ኢሕአድግ በፖለቲካ ልምድ እንዲሁም በህብረተሰቡ ተሰሚም ታዋቂም ስለነበር ገዚው ፓርቲ ምርጫውን በበላይነት ለማጠናቀቅ ሙሉ ዕምነት ነበረው ሆኖም ግን ወደ ምርጫው ቅስቀሳ ሲገባ እየታየ የመጣው ፈጽሞ ያልተጠበቀና ገዚው ፓርቲ የከፈተውን የዶሞክራሲ በር ለመዝጋት አስቸጋሪ የነበረበት እንዲሁም ወደ ኋላ ማፈግፈግ የማይችልበት ወቅት ነበር፡፡
በተቃዋሚዎች በኩል በወቅቱ የምሁሮች ስብስብ ተብሎ ሲሞካሽ የነበረው ቅንጅት የገዢው ፓርቲ ጠንካራ ተፎካካሪ ነበር ለዚህም ምክንያቶቹ በርካታ ቢሆኑም ድርጅቱ በውስጡ ጉምቱ የፖለቲካ አዋቂዎችን ማካተቱ ፤ ድርጅቱ በመረጃ የተደገፈ ጠንካራ ክርክር ማካሄዱ፤በምርጫ  ክርክሮች ወቅት ሚያቀርባቸው ተከራካሪዎች ኢሕአዴግ ከሚያቀርባቸው የተሻሉ መሆናቸው፤ የማህበረሰቡን የልብ ትርታን መሰረት ያደረጉ ጠንካራ ትችቶችን  በገዢው ፓርቲ ላይ በማቅረባቸው (የዘር ፓለቲካን  ፊትለፊት  በመተቸታቸው ፤ ሙስናን በመረጃ አስደግፈው በማጋለጣቸው፤ በገዢው ፓርቲ  የተንቋሸሸውን  ስራ አጥ ወጣቱን ስራ ፈጣሪ ለማድረግ ንድፈ ሃሳብ ማቅረቡ ከብዙ በጥቂቱ ሚጠቀሱ ናቸው) ፤ ዘርን መሰረት ያላደረገ  የፖለቲካ አቅጣጫ (political ideology) ይዞ መቅረቡ ፤ ድርጅቱ የተለያዩ የፖለቲካ ድርጅቶችን ያቀናጀ መሆኑና ሌሎች ምክንያቶች ተደማምረው የምርጫውን ግምት አፋልሰውታል፡፡
ኢሕአዴግን ለውድቀት የዳረጉ ውስጣዊ ምክንያቶች
ከላይ በጠቅላላው ለማሳየት እንደተሞከረው የምርጫ 97 ለተቃዋሚዎች የፈጠረውን እድልና ገዢው ፓርቲ ላይ ያስከተለውን አሉታዊ ተጽዕኖ ሲሆን ከዚህ በታች የምንመለከተው በድርጅቱ ውስጥ የነበረውን ውስጣዊ ችግሮችን ይሆናል፡
1.ከመጠን ያለፈ በራስ መተማመን
ኢሕአዴግ ከ1997 በፊት በነበሩት ምርጫዎች ተቀናቃኝ የነበሩትን በቀጥታ እንዲሁም በተዘዋዋሪ ካዳከማቸው ከፊሎችንም ከበታተነ በኋላ አስጊ የፖለቲካ ተቃዋሚ ስላልነበረ በምርጫ 97 ፍጹም የበላይነትን ለመቀናጀት እምነት ነበረው ለዚህም ማሳይው ከሌሎች የምርጫ ጊዜያቶች በተለየ ሁኔታ ለተቃዋሚዎች ሰፊ የአየር ሽፋን መስጠቱ ፤ የተለያዩ በርካታ የመከራከሪያ መድረኮችን ማዘጋጀቱ ፤ ክርክሮቹ ቀጥታ የአየር ሽፋን ማግኘታቸው ሲሆኑ ባልተጠበቀ መልኩ ጠንካራ ሆኖ የቀረበው ቅንጅት እንዲሁም ሌሎች ተቃዋሚዎች እድሉን በሚገባ ስለመጠቀማቸው በወቅቱ የነበረው የምርጫ ውጤት አመላካች ነው፡፡
2.ጠንካራ ተከራካሪ ያለማዘጋጀት
በተለያዩ የክርክር መድረኮች ኢሕዴግን ወክለው የሚቀርቡ ተከራካሪዎች ከተቃዋሚዎች ተሸለው ባለመገኘታችው እንዲሁም የሚያቀርቧቸው መከራከሪያዎች በመረጃ የተደገፉ አለመሆናቸውና  በተደጋጋሚ በተለያዩ የመንግስት ሚዲያዎች ሲሰሙ የቆዩ በመሆናቸው አሰልቺ ነበሩ፡፡ በወቅቱ በተቃዋሚዎች የሚቀርቡትን ፈታኝ ጥያቄዎች በበቂ ሁኔታ የሚመልስ ባለመኖሩ ኢሕአዴግ እየኮሰሰ ሌላው እየገነነ የመጣበት ሁኔታ እንደነበር የሁላችንም የቅርብ ጊዜ ትዝታ ነው፤፤
3.የአባላት ታማኝ አለመሆን
የተለያዩ መረጃዎች እንደሚያመለክተው ኢሕዴግ በ1997 ምርጫ ወቅት ጠቅላላ ከ6 ሚሊዬን በላይ አባላት የነበሩት ሲሆን ይህንን አባላት በማሰብ ገዢው ፓርቲ በቀላሉ እንደሚያሸንፍ መገመቱ ስህተት ላይመስል ይችል ይሆናል ነገር ግን ከምርጫው ማግስት ለመረዳት እንደተቻለው አብዛኛው አባላት የድርጅቱን የፖለቲካ ፕሮግራምን በመረዳት ሳይሆን የስራ ዕድል ለማግኘትና የተለያዩ ጥቅማ ጥቅሞችን በመፈለግ ፓርቲውን መቀላቀላቸው ነው፡፡ በአዲስ አበባ ድርጅቱ ድምጽ አገኝባቸዋለው ብሎ ባሰበባቸው በተክለሃይማኖት ፤ ቦሌ እና ሌሎች አካባቢዎች መሸነፉ አንዱ ማሳያ ሊሆን ይችላል፡፡
4.ሙስና
ኢሕአዴግ በዋነኛነት ከሚታወቅባቸው እኩይ ባህሪያቶቹ አንዱ ሙስና ሲሆን ይህም የሚከናወነው ፍትሃዊ በሆነ መልኩ ሳይሆን በተወሰኑ ቡድኖች ፤ ነባር ታጋዮች እንዲሁም ዘርን መአከል ያደረገ ስለነበር ሌሎች አጋር ድርጅቶች ውስጥ ውስጡን መከፋታቸው የነበረ ሲሆን ይህም መከፋት አባላቱ ሌሎች አማራጫ ፓርቲዎችን  እንዲመለከቱ ወይም ድርጅቱ ላይ የበቀል እርምጃ ለመውሰድ ከማነሳሳቱም በላይ ድርጅቱን የግላቸው አድርጎ ለማሰብ አዳጋች ነበር፡፡
ምርጫ 2002:- በዚህ ምርጫ ላይ ኢሕአዴግ ከ1997ቱ ምርጫ ብዙ የተማረበት እና በቂ ዝግጅት ያደረገበት ስለነበር ውጤቱን ለመቀልበት ችሎ ነበር፡፡ በዚህ ምርጫ ወቅት ድርጅቱ በአብዛኛ የፖለቲካ ተንታኞች ሲገለጽ እንደነበረው ብቻውን ሮጦ ብቻውን ያሸነፈበት ምርጫ ነበር፡፡ ለዚህም ምክንያቶቹ፡-
  • በምርጫ 97 ላይ ጠንካራ የነበረውን ቅንጅትን አከርካሪውን በመስበር የበላይ አመራሮቹን በማሰር እንዲሁም ከሀገር እንዲሰደዱ በማድረግ ፤ ህዝቡን ይቅርታ እንዲጠይቁ በማስገደድ በህዝቡ ውስጥ እምነት እንዳይኖራቸው በማድረግና በሌሎችም እኩይ የፖለቲካ ስራዎቹ ድርጅቱን በማዳከሙ /በማፈራረሱ
  • በራሱ በኢሕአዴግ የተፈጠሩ ተቃዋሚ ፓርቲዎችን በመፍጠር እንዲሁም ሌሎች ተቃዋሚዎች በኢሕአዴግ ሴራ እንዲሁም በግላቸው ምክንያት ከምርጫ እራሳቸውን ማግለላቸው
  • አጭር የክርክር መድረኮችን በማዛጋጀት እንዲሁም ለተቃዋሚዎች አጭር ጊዜ በመስጠት በተቃራኒው ለራሱ ሰፊ የአየር ሽፋን በመስጠት የድርጅቱን ፕሮግራሞች ማስተዋወቁ
  • በ1997 በቅንጅትና በሌሎች ተቃዋሚ ፓርቲዎች ይቀርቡ የነበሩ አማራጭ የልማት እስትራተጂዎችን በመውሰድና ከፊሎችንም በመተግበር ከተሰራው ስራ በላይ ፕሮፖጋንዳ በመስራት (ጥቃቅንና አነስተኛ ፤ ማህበራትን ማደራጀት ፤ ወጣቱን አደገኛ ቦዘኔ ከማለት ወደ ወጣት የልማት ሀይል መቀየር ፤ የጋራ የመኖሪያ ቤቶችን መገንባትና የመሳሰሉት ከምርጫ 1997 በፊት በገዢው ፓርቲ ተሰምተው የማይታወቁ ሲሆን ከምርጫ 97 በኋላ ጽንሰ ሀሳቡ ከተቃዋሚዎች ስለመሰረቁ ማሳይዎች ናቸው)
  • ቀደም ሲል ገጠርን ማዕከል ያደረገውን ልማት ወደ ከተማ በማምጣት የሚታዩ ለውጦችን በማቅረብ እነሱንም በመንግስት ሚዲያዎች አግንኖ ማቅረቡ (መንገድ ፤ ውሃ ፤ ኤሌክትሪክ ወዘተ)
  • የህዝቡ ተስፋ መቁረጥ፡ – በምርጫ 97 ወቅት በህዝቡ ተስፋ የተጣለባቸው ፓርቲዎች ከነአካቴው መጥፋታቸውና እነሱን ሊተካ የሚችል ጠንካራ ተፎካካሪ ፓርቲ መጥፋቱ
  • ጠንካራ የፖለቲካ ቅስቀሳ መደረጉ ፡ – መንግስት የተለያዩ መድረኮችን በማዘጋጀት የተሰሩ የልማት ስራዎችን በማቅረብ ፤ ህብረተሰቡን በማወያየት እንዲሁም ትልልቅ ካፒታል የሚጠይቁ ፕሮጀክቶችን በማስፋፋቱና የረጅም ጊዜ ዕቅዶችን በማቅረቡ
  • ምርጫ ቦርድ ላይ ያለውን ስውር እጅ በማስፋፋት ጠንካራ ክትትል ማድረግና የድርጅቱ የቀኝ ክንፍ መሆኑ በዚህና በሌሎች ምክንያቶች ገዢው ፓርቲ ሙሉ ለሙሉ የምርጫው አሸናፊ ሊሆን ችሏል፡፡ ከሁለቱ ተከታታይ ምርጫዎች የምንማራቸው አበይት ጉዳዮች ቢኖሩ፡
  • ኢህአዴግ በቢሊዮን የሚቆጠር የፋይናንስ አቅም እንዳለውና ለፖለቲካ ቅስቀሳ በቂ አቅም እንዳለው በተቃራኒው ተቃዋሚ ፓርቲዎች ያላቸው የፋይናንስ አቅም እጅግ አናሳ በመሆኑ በራካታ አባላትን ለማፍራት እንዲሁም ቅስቀሳዎችን ለማድረግ የአቅም ውሱንነት እንዳላቸው
  • ኢሕአዴግ የ1997ቱ ምርጫ ብዙ ልምዶችን የቀሰመበትና በወቅቱ አሳይቶት የነበረው የዲሞክራሲ ጭላንጭል በማጥፋት ፍፁም አምባገነን እየሆነ መምጣቱን
  • ኢሕአዴግ የተቃዋሚዎችን ደካማ ጎን በመጠቀም እንዲሁም የስለላ መረቦቹን በመጠቀም ተቃዋሚዎችን የማዳከምና የማፈረካከስ ልምዱን ያካበተ መሆኑን እና ፓርቲዎች ለምርጫ ከመድረሳቸው አስቀድሞ ከምርጫው እራሳቸውን እንዲያገሉ ጫና ማሳደሩን
  • የምርጫ ቦርድ መመሪያዎችንና ደንቦችን ኢሕአዴግ በፈለገው መልኩ ማሻሻሉንና ህጉ ለሁሉም በእኩል ደረጃ ተጠቃሚ የማያደርግ መሆኑንና እና ሌሎች በርካታ ጉዳዮች ናቸው፡፡እነዚህን እንደ መነሻነት በመጠቀም በምርጫ 2007 ሊገጥሙ የሚችሉትን ከወዲሁ ለመገመት ያህል፡ -
ኢሕአዴግ
በገዢው ፓርቲ በኩል ለምርጫው እየተደረጉ ያሉ ቅድመ ዝግጅቶች ከዚህ ቀደም ሲደረጉ ከነበሩት በእጅጉ የላቁ ናቸው፡፡ ይህም ነፃ የግል ፕሬሶችን ያለምንም በቂ ማስረጃ  በማሰር ፤ በመክሰስ ፤ በማስፈራራት ፤ እንዲሁም አገር ለቀው እንዲሰደዱ በማድረግ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ፕሮግራማቸውን  የሚያስተዋውቁበትን  መንገድ መዝጋቱ፡፡ ከዚህም  በተጨማሪ  ህዝቡ አማራጭ የመረጃ ምንጮች እንዳይኖሩት በማድረግ ህዝቡ በሚያገኘው አንድ አገራዊ የቴሌቪዝን ጣቢያ የገዢውን ልማታዊ ስራዎች ብቻ እንዲያይ ማድረጉ ነው፡፡
የተለያዩ የማህበረሰብ ድህረ ገፆች ላይ ፤ የደህንነት ሀይሎችን በማሰማራት እና ድንገተኛ ፍተሸዎችን በማድረግ ህዝቡን በማሸማቀቅ ፤ ሀይማኖትን ከሀይማት በማጋጨት ፤ የዘር ግጭቶችን በማቀነባበር ፤ ህዝቡ ላይ ሽብር በመንዛት ህዝቡ ከኢሕአዴግ ውጭ አማራጭ እንዳያስብ በማድረግ ህዝቡ እንዲመርጠው ብሎም ደግሞ የደህንነቱን ጡንቻ በማሳየት ለማስፈራራት በመሞከር ላይ ነው ለዚህም ማሳይው የተለያዩ የፖለተካ ስደተኞችን እና እንዲሁም በተለያዩ አገራት ይኖሩ የነበሩ የተቃዋሚ ድርጅት ቁልፍ ሰዎችን  አፍኖ በማምጣት ህዝቡ ላይ ፍራቻን ሲዘራ ይስተዋላል፡፡
ከዚህም በተጨማሪ እንደ ምርጫ 2002 ሁሉ ተቃዋሚ ፓርቲዎችን  በመከፋፈል ፤ በመታተን እንዲሁም በተለይዩ ምክንያቶች አመራሮቻቸውን በማሰር ተሳትፏቸውን ማዳከምን ተያይዞታል እንደ ማሳይም በአንድነት ለዲሞክራሲና ለልማት ፤ በአረና ፓርቲ እንዲሁም በሰማያዊ ፓርቲ ላይ እያደረሰ ያለው የማፈራረስ ፤ የማሸማቀቅ እንዲሁም እስራቶችን ማየት በቂ ማስረጃ ነው፡፡
የፖለቲካ ቅስቀሳዎችን በተመለከተም በአሁኑ ወቅት በሲቪል ሰርቫንቱ እና በዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች እንዲሁም በነዋሪው ላይ ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ በማፍሰስ ስልጠናዎችን እያካሄደ ሲሆን በተቃራኒው ደግሞ  ተቃዋሚ ፓርቲዎች የመሰብሰቢያ አዳራሾችን የመከራይት አቅም ማሳጣት  አቅም ያላቸውንም  ደግሞ የአዳራሽ፣ ቢሮ፣እንዲሁም  ኪራይ ቤቶች እንዳያገኙ ተጽዕኖ በመፍጠር  ላይ ነው፡፡
ተቃዋሚ ፓርቲዎች
በያዝነው ዓመት ማገባደጃ ላይ ለሚከናወነው አገራዊ ምርጫ ተቃሚ ፓርቲዎች እያደረጉ ያለው ቅድመ ዝግጅት በገዢው ፓርቲ ጥብቅ ክትትል ስር ሲሆን ፓርቲዎቹ የሚደርስባቸውን ጫና ለመቋቋም እንዲሁም ጠንካራ ተፎካካሪ ለመሆን እንዲያስችላቸው ውህደት ለመፈፀም በሂደት ላይ ሲሆኑ በገዢው ፓርቲ ስውር እጆች ምክንያት በሚፈለገው ፍጥነት እየተጓዘ እንዳልሆነ እያየን ነው፡፡ በዚህ ምርጫ በሃገር ውስጥ ትልቅ  ግምት ከሚሰጣቸው እንደ አንድነት እና ሰማያዊ ፓርቲ  በገዢው ፓርቲ ተደጋጋሚ ትንኮሳ እየደረሰባቸው ሲሆን ይህም የምርጫው ዋዜማ ላይ ሊበረታ እንደሚችል ይገመታል፡፡
ህብረተሰቡ
ካለፉት የምርጫ ጊዜያቶች በተለየ ሁኔታ ማሕበረሰቡ የፓለቲካ አድማሱ የሰፋበት ሆኔታ ሲሆን ለዚህም አበይት ምክንያቶቹ በማሕበራዊ ድህረ ገፆች የሚለቀቁ የተለያዩ አክቲቪስቶችን  ንግግር ፤ ክርክሮች ፤ በግል ፕሬሱ ይታተሙ የነበሩ የፖለቲካ ትንታኔዎች ፤ ከገዢው ፓርቲ እየሾለኩ የሚወጡ የተለያዩ መረጃዎች እንዲሁም ህብረተሰቡ አማራጭ የመረጃ ምንጭ በማግኘቱ ነው፡፡ በመሆኑም ማሕበረሰቡ ምርጫው በገዢው ፓርቲ የተለመደ ማጨበርበሮች ሊጠናቀቅ እንደሚችል ግምቱ ቢኖረውም እንደ ባለፉት የምርጫ ጊዜያቶች በቸልታ ያልፈዋል ተብሎ አይታሰብም ምክንያቱም ህዝቡ መንግስት የሚያደርገውን የመብት ረገጣ ፤ አድሎአዊ አገዛዝ ፤ ሙስና ፤ እንዲሁም በእስልምና ሀይማኖት እና በኦርቶዶክስ የዕምነት ተከታዮች ላይ እጁን በማስገባት እየፈፀመ ያለውን በደል በሚገባ ስለሚያውቅ ድርጅቱ ጉልበት ያለው ቢመስልም ውስጡ ግን ባዶ ፤ ደጋፊ ያለው ቢመስልም አባላቱ በጥቅም ፤ በዘር እንዲሁም በመልካም አስተዳደር እጦት ያኮረፉ የሚበዙበት ሲሆን ገዚው ፓርቲ ከሕወሓት ውጨ ያሉ ፓርቲዎችን በአይነ ቁራኛ መመልከቱና አብዛኛውን ስልጣን ጠቅልሎ መያዙ በአጋር ድርጅቶች ጥርስ ውስጥ እንዲገባ ምክንያት ሆነዋል፡፡
ማጠቃለያ
የምርጫውን ውጤት ከወዲሁ መተንበይ ባይቻልም በገዢው ፓርቲ ውስጥ ያሉ አባላት   በወያኔ ሕወሓት ላይ በተለይዩ ምክንያቶች ውስጣቸው የሻከረ በመሆኑ (ብአዴን በግንቦት 7 ፤ ኦሕዴድ በወጣት ተተኪዎቹ የስልጣን ይገባናል ተደጋጋሚ ጥያቄዎች ፤ እንዲሁም በሌሎች አጋር ፓርቲዎች) የምርጫውን ውጤት ወዳልተገመተ አቅጣጫ ሊመሩት እንደሚችል ይገመታል፡፡ የማሕበረሰቡ ንቃተ ህሊና መጨመር ፤ ገዢውን ፓርቲ በተጨባጭ መረጃዎች መወንጀል መጀመሩ ፤ መንግስት በተደጋጋሚ የሚፈፅማቸው የሰብዓዊ መብት ረገጣዎች ፤ የአገሪቱን ከፍተኛ ቁጥር የሚሸፍኑትን አንጋፋ የሀይማኖት ተቋማትን ማስኮረፉ ከሀይማኖቱ ተከታዮች የምርጫ ካርድ ሊነፈግ እንደሚችልም  ይገመታል ይሁንና ገዢው ፓርቲ በምርጫ ቢሸነፍም ስልጣኑን ለመልቀቅ ፍቃደኛ ባለመሆኑ ድምፁ የተሰረቀበት ማሕበረሰብ አልመረጥኩም ብሎ በጥያቄ  ተቃውሞ ቢነሳ  ተቃውሞውን በበቂ ሁኔታ የሚያስተባብርና ሀላፊነቱን የሚወስድ ፓርቲ ባለመኖሩ አገሪቷን ወደ አላስፈላጊ ዕልቂት እንዳይጥላት ያሰጋል፡፡ ገዢው የወያኔፓርቲ የምርጫውን ውጤት በጸጋ ተቀብሎ ለመጪዋ ኢትዮጵያ ዘላለማዊነት በቅን ልቦና ምርጫውን ለግል ጥቅም ሳይሆን የህዝቡን ድምፅ እንዲያከብር ልባዊ  ምኞቴ ነው፡፡
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር
Dagnachew Tegegne

Wednesday, November 12, 2014

አቃቢ ህግ በጦማርያኑና ጋዜጠኞቹ ላይ የመሰረተውን ክስ እንዲያሻሽል ታዘዘ

ክሱ ተሻሽሎ መቅረቡን ለማየት ለህዳር 24 ቀጠሮ ተሰጥቷል
በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር
የፌደራል አቃቢ ህግ በእነ ሶልያና ሽመልስ የክስ መዝገብ በጦማርያኑና በጋዜጠኞቹ ላይ የመሰረተውን የሽብር ክስ እንዲያሻሽል የልደታ ከፍተኛ ችሎት ትዕዛዝ ሰጠ፡፡

ፍርድ ቤቱ ዛሬ ህዳር 3/2007 ዓ.ም በዋለው ችሎት ቀደም ብሎ የተከሳሽ ጠበቆች ያቀረቡትን የክስ መቃወሚያ መርምሮ ብይን በመስጠት በንባብ አሰምቷል፡፡ በዚህ መሰረትም ፍርድ ቤቱ በክስ መቃወሚያው ላይ የቀረቡትን ዝርዝር ነጥቦች መርምሮ በተወሰኑ ነጥቦች ላይ አቃቢ ህግ ክሱን እንዲያሻሽል ትዕዛዝ ሲሰጥ፣ በሁለተኛነት ቀርቦ የነበረው የክስ ይዘት በአንደኛው የክስ ይዘት ላይ መጠቃለል ስለሚችል ሁለተኛውን የክስ ይዘት ፍርድ ቤቱ ሙሉ ለሙሉ ውድቅ አድርጎታል፡፡
በክስ ዝርዝሩ ላይ ተከሳሾቹ ‹‹ለአመጽ ማነሳሳትና መምራት›› የሚያስችል ስልጠና ወስደዋል በሚል በተጠቀሰው ላይ ስልጠናው መቼ፣ በማን እና በምን ጉዳዮች ላይ ተሰጠ የሚለው ግልጽ ስላልሆነ አቃቢ ህግ ክሱን እንዲያሻሽል ተጠይቋል፡፡
በተጨማሪም ተከሳሾቹ አመጽ ለመምራት የስራ ክፍፍል አድርገዋል በሚል የተጠቀሰባቸው የክሱ ይዘት ‹‹ምን አይነት የስራ ክፍፍል፣ ማን ምን እንዲሰራ ክፍፍሉ ተደረገ›› የሚለውን ስለማያመለክት ይህንንም መሻሻል እንዳለበት ፍርድ ቤቱ ወስኗል፡፡
በተጨማሪም በክሱ ዝርዝር ላይ ‹‹ቡድን›› እና ‹‹ድርጅት›› በሚል (ግንቦት 7፣ ኦነግ ወይስ ሌላ የሚለውን ስለማይገልጽ) በደፈናው የቀረቡት ነጥቦች ላይ በዝርዝር መቀመጥ ስላለባቸው አቃቢ ህግ ማሻሻያ እንዲያደርግ ታዝዟል፡፡
በሌላ በኩል የተከሳሽ ጠበቆች ‹‹በኢሳት ሬድዮና ቴሌቪዥን መረጃ በመስጠት›› በሚል ተከሳሾች ላይ የቀረበው የክስ ይዘት ሆን ተብሎ ወደ ሌላ አካል (ግንቦት 7) ጋር ለማገናኘት ነው በሚል ያቀረቡትን መቃወሚያ፣ ‹‹በኢሳትና በግንቦት 7 መካከል ያለው ግንኙነት ወደፊት በማስረጃ የሚታይ ነው በሚል ፍርድ ቤቱ መቃወሚያውን ውድቅ አድርጎታል፡፡
ከተከሳሽ ጠበቆች መካከል የሆኑት አቶ አምሃ መኮንን ከችሎቱ በኋላ ለጋዜጠኞች እንደተናገሩት፣ ፍርድ ቤቱ በተከሳሽ ጠበቆች ላይ የቀረበውን የክስ መቃወሚያ ጊዜ ወስዶ መርምሮ ውሳኔ እንዳሳለፈ ጠቅሰዋል፡፡ ይሻሻላሉ የተባሉት የክሱ ይዘቶች ላይ ጥያቄ የተነሳላቸው አቶ አምሃ የውሳኔው ዝርዝር በጽሑፍ ገና እንዳልደረሳቸው ጠቅሰው፣ ‹‹አቃቢ ህግ በታዘዘው መሰረት ክሱን የማያሻሽል ከሆነ ይሻሻላሉ የተባሉት የክሱ ይዘቶች ውድቅ የሚሆኑበት አሰራር አለ›› ብለዋል፡፡
ፍርድ ቤቱ ክሱ ተሻሽሎ መቅረብ አለመቅረቡን ለማየት ለህዳር 24/2007 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጥቷል፡፡
zehabesha