Friday, February 28, 2014

Co-Pilot Hailemedhen Needs Protection !!

Ethiopians in Norway Bern held demonstration to ask the Switzerland government grant asylum to the Ethiopian Airlines Co-pilot Hailemedehin Abera who took the Ethiopian Airlines plane Boeing 767 to Switzerland and landed peacefully.

Thursday, February 27, 2014

በትንሹም ቢሆን የበኩላችንን ማደረግ ይጠበቅብናል::

 ረዳት አብራሪ ሃይለመድህን አበራ Boeing  767 -ET 702 ይዞ ከ ሮም ወደ ጄኔቨ ሲአቀና ማንም መንገደኛ ምን እየተክናወነ እንዳለ ያወቀም  የተረዳም አለነበረም :: ጄኔቨ ሲደርስ ዋናው አብራሪ ነገሩን ሲገልጽ, ሃይለመድህን በገመድ በመስኮት ሲወርድ ,ፓሊስ እጅ በጭንቅላት ሲል ግማሹ መደናበር ግማሹ ማወቅ ጀመረ ::  ይሄኔ ነው አለም ሰለ ጠለፋው ባአንዴ ያዳረሰቺው :: በሙሉ የዜና አውታሮች ዘገቡት አራገቡት መረመሩት አወጡት አወረዱት ልጁ እውነት ነው ያለምንም መሳሪአ በሰላም ከብቃት የማብረር ችሎታ ጋር ጄኔቨ ያሳረፋት::   ለዚ ነው ተሳፋሪወ የትገረመውና የተደናበረው::  BBC,CNN ,AL JAZEERA , FRANCE 24 ,ZEHABESHAW ,FACEBOOKU ,..........ወዘተ ::ባንዴ ብቻ አዳረሱት  እውነት ነው ሲአወሩትም እንደነበረው ልጁ የኢኮኖሚ ችግር: የጤና እንዲሁም ከማህበረሰቡ ጋር ችግር  አልነበረበተም :: ችግሩ አንድ እና አንድ ነው :: በሱና በሃገሩ ልጆች ላይ የሚደርሰው ጫና : ጭቆና : ያንድ የብሄር ተዋጾ የበላይነት የነገሰበት ስርአት......................አስደስቶት ነው አልልም   : :የልጁ ምክንያት ምን እንደሆነ ባያስቀምጡትም እሱም ስላልተናገረ በወያኔ መንግስት ግን  በግልጽ የሚታይ የህዝብ ጭቆና እንዳለ አረጋግጠው አልፈውልናል: : ይህ ረዳት አብራሪ በጄኔቨ የጥገኝነት ጥያቄ አቅርቦ ጉዳዩ ክህግ አኩአያ እየታየ ነው :: የሲዊዝ መንግስት ረዳት አብራሪወን ሃይለመድህን አበራን አሳልፎ ለኢትዮጵያ መንግስት እንዳይሰጥ በተለያዩ አገሮች ሰላማዊ ሰልፍ ይደረጋል ወንድማችን ያገራችንን ጭቆና በራሱ መንገድ እንዲህ አጋልጡአል:: እኛም ከሱ ወገን መሆናችንን በፓለቲካው  በትንሹም ቢሆን የበኩላችንን  ማደረግ ይጠበቅብናል::

Sunday, February 23, 2014

ህዝቡ ከባዶ ጭንቅላት ባዶ እግር ይሻላል ሲል ለብአዴን/ኢህአዴግ ተቃውሞን አሰማ።

አማራው ክልል ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አለምነው መኮንን የሚመሩትን የአማራ ሕዝብ በጸያፍ ቃላት መሳደባቸውን ተከትሎ አንድነት እና መኢአድ ፓርቲዎች በጋራ ዛሬ በባህርዳር የጠሩት ሰላማዊ ሰልፍ ከፍተኛ የሆነ ሕዝብ በተገኘበት በሰላም ተጠናቀቀ።
ህዝቡ ከባዶ ጭንቅላት ባዶ እግር ይሻላል ሲል ለብአዴን/ኢህአዴግ ተቃውሞን አሰማ።
ሺህዎች የሚቆጠሩ የባህርዳር ነዋሪዎች ቁጣቸውን ለመግለጽ በወጡበት በዚህ ሰላማዊ ሰልፍ ሕዝቡ በአቶ አለምነው የተሰደበውን ለማስታወስና ቁጣውንም ለመግለጽ ሰልፈኛው ጫማውን አንገቱ ላይ በማንጠልጠል በሰላማዊ ሁኔታ በባዶ እግሩ በመሄድ በአዲስ የተቃውሞ ስልት ድምጹን አሰምቷል ያሉት በስፍራው የነበሩ የሰልፉ ታዳሚዎች እንዲህ ያለው የትግል አገላለጽ የሚደነቅና ወደፊትም ሊበረታታ የሚገባው ነው ብለዋል።
በባህር ዳር በተደረገው በዚህ ትልቅ የተቃውሞ ሰልፍ ላይ አቶ አለምነው በአማራ ህዝብ ላይ የተናገሩት የጥላቻ ንግግር በትላልቅ ስፒከሮች ለሰልፈኛው በድጋሚ የተሰማ ሲሆን ሰልፈኛውም በቁጭት በብአዴን ላይ ተቃውሞውን በአንድ ድምጽ አሰምቷል።

Saturday, February 15, 2014

የመኖሪያ ፈቃድ – ከራስ ወዳድነት ያልራቀው የስደተኞች የመጨረሻ ግብ


oslo 9
በተቃራኒው ደግሞ ብር ካየ የሚገባበትን ጉድጓድ፣ የሚፈጽመውን ጥፋት የማይለካው ኢህአዴግ የሚመራት ኢትዮጵያ ያፈራቻቸው ስደተኞች ኖርዌይን ተጠልለዋል። ከአራት ሺህ በላይ ወገኖች ኖርዌይ በጡረታ መልክ እየቆረሰችላቸው ወይም ስራ እየሰሩ ህይወታቸውን ይመራሉ። በኖርዌይ መወልወያና መጥረጊያ ይዘው ቀን የሚገፉ “ራፐሮች”፣ አዛውንቶችን የሚንከባከቡ ሞግዚቶች፣ በከፍተኛ የትምህርት ተቋማትና የስራ እርከን የሚሰሩ ባለሙያዎች አንዲሁም በስደተኞች ካምፕ ተጠልለው የመኖሪያ ፈቃድ የሌላቸው ወገኖች በየዘርፉ በብዙ መልክ ተመድበው ይኖራሉ።
አብዛኞቹ የመኖሪያ ፈቃድ ባለቤቶች ከፖለቲካ ድርጅቶችና ከሲቪክ ማህበራት በተሰጣቸው የአገልግሎት የድጋፍ ደብዳቤና ክትትል ቢሆንም መልስ ካገኙ በኋላ ወገናቸውን መልሶ ከመርዳት የውሃ ሽታ ሆነው እንደሚቀሩ ይነገራል። “በኢትዮጵያ አምላክ ያዙኝ ልቀቁኝ” በማለት የትግል ችቦ ለኳሽ፣ አቀጣጣይ፣ መሪና አስተናባሪ መስለው የሚፈልጉትን እስኪያገኙ በርተው ስለሚጠፉ በድፍረት የሚነሳ obang 2ጉዳይ ባይሆንም አቶ ኦባንግ ሜቶ አምርረው የተናገሩበት ጉዳይ ነበር። እዚህ ላይ ሊሰመርበት የሚገባው ትልቅ ጉዳይ የመኖሪያ ፈቃድ በነበራቸውም ሆነ ባልነበራቸው ወቅት ወገኖቻቸውን፣ አገራቸውን እንዲሁም ቃል ኪዳናቸውን ሳይዘነጉ ባሉበት የዓላማ አለት ላይ ሆነው ስራቸውን የሚሰሩ ምርጦችም የመኖራቸው እውነት ይሆናል።
እንቁራሪትን ጨምሮ ለውሃ ውስጥ ነዋሪዎች በመቆረቆር እኛ ለዘመናት አልከፈትም ያለንን የነዳጅ ጉድጓድ በዘጋችው ኖርዌይ ውስጥ የስደት ማመልከቻቸው ተቀባይነት በማጣቱ እድሜያቸውን በካምፕ ውስጥ የሚያሳልፉ የሰው ልጆች ቁጥር ቀላል አይደለም። ከእጅ ወደ አፍ በሆነች የኪስ ገንዘብ ካምፕ ውስጥ ከሚኖሩትን ወገኖች መካካል ለስነልቦና ችግር የተጋለጡ፣ በችግር ምክንያት በቴዲ አፍሮ “ምን ይዤ ልመለስ…” ዘፈን እያለቀሱ ኑሯቸውን የሚገፉትን ወገኖች ጥቂት አይደሉም። እኒህን ወገኖች አሰባስቦ ለመርዳትም ሆነ ለማወያየት ቢችግርም፣ ችግሩ ሳውዲ እንደደረሰው አይነት ባይሆንም ቸል ሊባል የሚገባው አይሆንም። አቶ ኦባንግ ይህንን ጉዳይ ያነሱት “ራሳችንን አስቀድመን እናክብር” በሚል ነበር። እንደ እሳቸው አባባል ራስን የማክበርና ለራስ የመታመን ችግር የዛሬው የፖለቲካ ቀውስ ውጤትም ነው። ኢህአዴግ ራሳቸውን የማያከብሩትን በመሰብሰብ 22 ዓመት የገዛው ጠንካራ ሆኖ ሳይሆን ራሳቸውን ማክበር ያቃታቸውን በሆዳቸው በመደለል ነው። ዛሬም በስደት ምድር ራስን የማክበርና በነበሩበት ቦታ ያለመገኝት ተራ ብላጣ ብልጥነት አገር ቤት ካሉት ኦህዴድ፣ ብአዴን፣ ደህዴን … በተለየ ቦታ የሚያስቀምጥ አይሆንም።
ባለፈው ቅዳሜ ኦስሎ በተካሄደው ታላቅ ስብሰባ ዋናው ጉዳይ በሳዑዲ አረቢያ አገዛዝ አንጋቾችና አክራሪ ጽንፈኞች አማካይነት ዘግናኝ በደል ለተፈጸመባቸውና ለተፈናቀሉ ወገኖች የእርዳታ ገንዘብና ቁስ ማሰባሰብ ነበር። በዚሁ ስብሰባ ላይ ከኦነግና ከኦጋዴን ነጻ አውጪ ተወካዮች በስተቀር ሁሉም ተገኝተዋል። የተለያዩ የክርስትና ሃይማኖት ተቋማት፣ የእስልምና እምነት ተወካይ፣ የኢህአፓ፣ የኖርዌይ ድጋፍ ሰጪ ፎረም፣ የኖርዌይ የስደተኞች ማህበር፣ ተወካዮች በየተራ ንግግር አድርገዋል። ስብሰባውንና ሃሳቡን በማራመድ ግንባር ቀደሙን ሚና የተጫወተው የዝግጅቱ ባለቤት በኖርዌይ የኢትዮጵያ ስደተኞች ማህበር ሰብሳቢ አቶ ፋሲካ ባደረጉት ንግግር የተጀመረው ስብሰባ ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ዋና ዳይሬክትር አቶ ኦባንግ ሜቶ ነበሩ።oslo10
አቶ ፋሲካ የኖርዌይ ማህበረሰብ ዘወትር ለሚቀርብለት ጥያቄ አፋጣኝ መልስ እንደሚሰጥ በመጥቀስ አመስግነው የወቅቱን አሳሳቢ ሁኔታ በሚገባ አብራርተዋል። ስቅላት፣ አስገድዶ መድፈር፣ እስር፣ ግድያና ስቃይ እጣ ፈንታቸው ለሆኑት ወገኖች ድምጽ ከመሆን ጀምሮ የተለያዩ የአጋርነት መገለጫ ዝግጅቶች ላይ ማህበራቸው መገኘቱን ያመለከቱት አቶ ፋሲል “ድምጽ ለሌላቸው ድምጽ ከመሆን አልፈን በቁስና በገንዘብ ልንደጉም፣ አለን ልንል፣ አለንታነታችንን ለመግለጽ ስንነሳ ሰፊ ስራ ሰርተን ነው” በማለት በዕለቱ የተገኙትን የተለያዩ ተቋማት ወኪሎችን አወድሰዋል። የሚሰበሰበውንም ገንዝብ ለግሎባል አሊያንስ በማስረከብ እርዳታው ለወገኖች እንዲደርስ ሰፊ ውይይት መደረጉን ጠቁመዋል። ይሁን እንጂ ገንዘቡ የተለያዩ ተቋማትና ግለሰቦች በመሆኑ የገንዘቡን ባለቤቶች ውሳኔ የሚጠይቅ በመሆኑ ውሳኔውን አክብረው አፈጻጸሙን ተግባራዊ እንደሚያደርጉ በሚመሩት ማህበር ስም አመልክተዋል። በስብሳበው ላይ የተገኙት የፖለቲካ ድርጅቶች “ስለ ኢትዮጵያዊነት የሚያገባቸው ብቻ ናቸው” ሲሉም ገልጸዋል።
በይፋ ለመቋቋም አዲስ 22 ዓመት የፈጀበትና የዛሬ ሁለት ዓመት በይፋ የተመሰረተው የቃል ኪዳን ታቦት የፈውስ አገልግሎት አገልጋይና መሪ የሆኑት ወ/ሮ ሰዋሰው “ዓላማችን የታረዘን ማልበስ፣ የተጠማን ማጠጣት፣ የተራበን መመገብ፣ የታሰረን መጠየቅ በመሆኑ እንደ አንድ ኢትዮጵያዊ ምን ማድረግ ይገባኛል በማለት አስብ በነበረበት ጊዜ እንዲህ ያለው ስራ መሰራቱን ሰማሁ። አዲስ ከምንጀምር የተጀመረውን ለምን አንረዳም? በማለት መጣሁ” በማለት መልዕክታቸውን ጀመሩ። መጽሃፍ ቅዱስ እንደሚለው በማለት ወገኖችን ስለመርዳት ያስተማሩት ወ/ሮ ሰዋሰው፣ “ጌታ ኢየሱስ ሲመጣ ይህንን ያህል ጉባኤ ተሳትፌያለሁ። በብዙ ሱባኤ ተግኝቻለሁ … የሚል መልስ አያረካውም” ሲሉ መረዳዳት አስፈላጊ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል። በማያያዝም ዛሬ ቤተ ክርስቲያን ወገኖቿን ለመርዳት ስትነሳ፣ የፖለቲካ ተቋማት ወገኖቻቸውን ለመርዳት ሲነሱ እየተከታተሉ ማውገዝ አግባብ እንዳልሆነም አመልክተዋል።
ባለፉት 22 ዓመታት የክፋት መንፈስ አገራችንን እንደጎዳት ያመለከቱት ወ/ሮ ሰዋሰው፣ “የጻድቅ አይን ወደ ራሱ ይመለከታል” ተብሎ እንደተጻፈው አሁን ያለው ችግር ሲነጋ በእኛም ላይ መልኩን ቀይሮም ቢሆን ሊከሰት እንደሚችል አመልክተዋል። ሲጨርሱም “በሰው አገር ላይ ነን እኛም ላይ የሚደርሰው አይታወቅም። የቆመ የሚመስለው እንዳይወድቅ ይጠንቀቅ” በማለት ለቀረበላቸው አስፈላጊውን ሁሉ ለማድረግ ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።
የቅዱስ ገብርኤልና አቡነ ተ/ሃይማኖት ቤተክርስቲያንን በመወከል የተናገሩት ወ/ሮ ሂሩት ወርቁ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ሁሌም ከልጆቿ ጋር ተለይታ እንደማታውቅ የቀደመው ታሪኳ እንደሚመሰክር አስምረውበታል። አሁንም በተመሳሳይ ይህንኑ በጎ ስራ እንደሚገፉበትና የርዳታው ማሰባበሰብ በቤተክርስቲያን ደረጃ እየተሰራ እንደሆነና የተሰበሰበውንም ገንዘብ በወቅቱ እንደሚያስረክቡ አመልክተዋል። በመጨረሻም ለዚህ በጎ ስራ የተሰማሩትንና ፈቃደኛ የሆኑትን በሙሉ በረከትን ተመኝተውላቸዋል።
oslo 3ከኢትዮጵያ የ7ኛው ቀን አድቬንቲስት ቤ/ክ ህብረት የተወከሉት ዶ/ር ዙፋን አግደው በበኩላቸው ወገኖችን ለመርዳት በተጠራው ስብሰባ ላይ መገኘታቸው እንዳስደሰታቸው አመልክተዋል። በተለያዩ የበጎ ተግባራት ቤተ ክርስቲያናቸው ስትሳተፍ እንደቆየች ያወሱት ዶ/ር ዙፋን “ኢትዮጵያ እጆቿን ወደ እግዚአብሔር ታነሳለች በሚል እንደተጻፈው ጸሎታችን አንዲሰማ አንድ መሆን ያስፈልጋል” በማለት በህብረት የመሰባሰቡ ቁልፍ የልብ አንድነት መፍጠር ላይ እንደሆነ ገልጸዋል። “የእግዚአብሔር ቃል ሁለት ያለው ምንም ለሌለው እንዲሰጥ ያዛልና በርዳታው በኩል ነቅተን እንሳተፋለን” ሲሉ የወከሉትን ቤ/ክ አቋም አንጸባርቀዋል።
የኢህአፓ ተወካይ አቶ ምናሴ “ለዚህ ሁሉ አሳፋሪና አንገት የሚያስደፋ የወገኖቻችን ስቃይ ተጠያቂ ወያኔ ነው” ሲሉ የችግሩን ግዝፈት አመልክተዋል። የዲሞክራሲ ለውጥ ድጋፍ በኖርዌይ ተወካይ አቶ አቢ አማረ በተመሳሳይ የችግሩን አሳሳቢነትና አገር ቤት ስልጣንን በሃይል ያዘውን የኢህአዴግ አገዛዝ እጅ ለእጅ በመያያዝ መታገል በዋናነት አስፈላጊ መሆኑንን ጠቁመው በሳዑዲ አረቢያ ለተፈናቀሉ በሚደረገው ድጋፍ ላይ ድርጅታቸው የዘወትር ድጋፉን እንደሚገፋበት አረጋግጠዋል። በድርጅት ያልታቀፉ በድርጅት ጥላ ስር እንዲደራጁ ጥሪ አቅርበዋል። የኢትዮጵያ ስደተኞች ማህበር ተወካይ አቶ ሃምሳሉ በበኩላቸው ተመሳሳይ የትብብር ማረጋገጫ ሰጥተዋል።
የኢትዮጵያ የጋራ መድረክ ፎረም በኖርዌይን በመወከል ወ/ሮ ዙፋን አማረ ሲናገሩ “አንዳንዴ  ምነው በአባቶቼና በአያቶቼ ዘመን ምነው በተፈጠርኩ እላለሁ” በማለት የቀድሞው ዘመን ኢትዮጵያዊነትን ከአሁኑ ዘመን አንገት አስደፊው ማንነታችን ጋር አዛምደው ተናግረዋል። ይህ ትውልድ እጣው ውርደት እንደሆነ ያመለከቱት ወ/ሮ ዙፋን፣ ከዚህ ውድቀትና ሃፍረት ላይ ከጣለን ስርዓት እስከወዲያኛው ነጻ ለመውጣት እሳቸው ወከሉት ድርጅት እየሰራ መሀኑንና የሁሉም ህብረት አስፈላጊ መሆኑንን አስታውሰዋል።
“የቁርጥ ቀን ልጅ፤ የኢትዮጵያ እውነተኛ ልጅ፣ ንጹህ ኢትዮጵያዊ፣ ኢትዮጵያዊያን በተቸገሩበት ቦታ ሁሉ ቀድሞ የሚደርስ፣ …”፤ “የጥቁሩ ሰው” ስም ኦባንግ ሜቶ ተባለ። ኦባንግ ተነሱ። አስቀድመው ንግግር አድርገው የነበሩትን ሴት እህቶች “አከብራለሁ” አሉ። በመቀጠል በሳዑዲ ወገኖቻችን ላይ የደረሰውን ጉዳይ አስረዱ። በመቀጠልም ንግግራቸውን ወደ ስደተኛው አዞሩት “ፎቶ ከኔ ጋር ትነሳላችሁ፤ መልስ ስታገኙና የመኖሪያ ፈቃድ ስታገኙ አትታዩም፤ ትጠፋላችሁ” በማለት ፊት ለፊት ወቀሳቸውን ሰነዘሩ። በመሪነትና አቅጣጫን በሚያመላክት ሞገስ አጽንኦት ሰጥተው የተናገሩት አቶ ኦባንግ “ድክመት አለባችሁ” ብለዋል።
በኖርዌይ የመኖሪያ ፈቃድ ተከልክለው በስደት ካምፕ ውስጥ ያሉት ወገኖች በምን ደረጃ እንዳሉ አስታወቁ። የአእምሮ፣ የስነልቦናና የኢኮኖሚ ችግር እየተፈራረቀባቸው ዓመታት አንድ ቦታ ተቀምጠው መኖራቸው “እንዴት እረፍት ይሰጣል” ሲሉም ጠየቁ። “እናንተ ትናንት በተመሳሳይ ችግር ላይ የነበራችሁ፤ ዛሬ ወረቀት ስላገኛችሁ የቀድሞውን ማንነታችሁን ረሳችሁ” ሲሉ ሲሳካላቸው የሚሸሹትንና ወገኖቻቸውን የሚዘነጉትን አወገዙ። ከአጠቃላይ የወቅቱ ችግር ጋር በማያያዝ ‘ሰዎች ንን ራሳችንን እናክብር። አሁን የሚታዩት ችግሮች በሙሉ ራስን የማክበር ችግር ነው። እባካችሁን ራሳችሁን አክብሩ” ሲሉ መከሩ።
“ወያኔዎች ስራቸውን ያወቃሉ። እኛ ግን ስራችንን አናውቅም። በረሃ ሲገቡ ትግራይን ነጻ ለማውጣት ነበር ። እኔንና እናንተን የሚመስሉት ወንድሞቻችንና እህቶቻችን ራሳቸውን ማክበር ባለመቻላቸው ለትንሽ ዳቦ ጫካ ውስጥ የገቡት ወያኔዎች ትልቁን ዳቦ አገኙት” ሲሉ ከላይ ያነሱትን ሃሳብ አብራሩ። በስደት ኖርዌይ ከመጡ በኋላ ኦስሎን አንኳ የማያውቁ ወገኖችን ጉዳይ ደጋግመው ያነሱት አቶ ኦባንግ “እኔ ብለን ስንጀምር ነገር ይበላሻልና እኛ ብለን እንጀምር” ሲሉ ስለ ብሔር መከፋፈል ጣጣ መልዕክት ሰጥተዋል።obang 1
“አዲሲቷን ኢትዮጵያ ስንገነባ ሁሉን አስረን አንችልም። ዓለማችንም አይደለም” ያሉት ጥቁሩ ሰው፣ የስደት ምድር ጊዚያዊ ማረፊያ እንጂ የዘላለም አገር አይደለምና የራሳችን አገር ባለቤት ለመሆን በውስጣችን ያለውን ተንኮል እናስወግድ ብለዋል። በነጻነት እቅዳችን ውስጥ የሚበድሉንን ጨምሮ ሁሉንም ነጻ የማውጣት ስራ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ መሆኑንን ያወሱት ኦባንግ ሜቶ “በሳዑዲ የሌሎች አገራት ዜጎች መንግሥታቸው ሲሰበስባቸው የእኛ ዜጎች ግን እንደ ቅያሪ ጎማ በሌላ ይተካሉ በሚል ወገንና አገር አልባ እንደሆኑ ተቆጥረዋል። ከዚህ በላይ የከፋ ውርደት የለምና አሁንም በድጋሚ የምነግራችሁ ራሳችሁን በማክበር ለወገናችሁ ምላሽ ስጡ” በማለት የፊልም ምሳሌ በመስጠት ንግግራቸውን አጠቃለዋል።
“ይህ ፊልም የወኖቻችን ስቃይ የተቀረጸበት ነው። ፊልሙ ብርሃን የያዘውን ምስል ለመመልከት ብርሃን ይፈልጋል። ፊልሙ ብርሃን ካላገኘ ምስሉ ሊታይ አይችልም። ብርሃን ከላገኘ በጨለማ ውስጥ እንዳለ ይቀራል። እናንተም በጭለማ ውስጥ ላሉት ወገኖቻችሁ ብርሃን መሆን አለባችሁ። አገራችን ብርሃን የሚሆኑላት ትፈልጋለችና!!” አቶ ኦባንግ የስደተኞችን ጉዳይ በመያዝ አግባብ ካላቸው የኖርዌይ ባለስልጣናት ጋር ተነጋግረዋል። አቶ ኦባንግ በሚቀጥለው ወር ከኖርዌይ ጠቅላይ ሚኒስትር በቀረበላቸው የውይይት ጥያቄ መነሻነት ወደ ኖርዌይ ተመልሰው ይመጣሉ ። አቶ ኦባንግ ባለፉት ስድስት ወራት በድርጅታቸው አማካይነት ስለሰሩት ስራና አጠቃላይ እንቅስቃሴ አስመልክቶ ከጎልጉል ጋር ሰፊ ቃለ ምልልስ እንደሚያደርጉ ቃል በመግባት የሚከተለውን ተናግረዋል። “አሁን ነገሮች መልክ የያዙበት ወቅት ላይ እየተቃረብን ነው። ዜጎች ራሳችሁን በማክበርና ከክፋት ልቡናቸውን በማጽዳት ይደግፉን። የተቀረውን እኛ እንሰራዋለን፡፡” 

Friday, February 14, 2014

የጅዳ ቆንስል ሃላፊ ዘነበ ከበደ ከኃላፊነታቸው ተነሱ! ለጊዜው በቆንስል ሸሪፍ ከይሩ ይተካሉ ተብሏል



foto
* ትናንት ረፋዱ ላይ በገደምዳሜ  “ጉልቻ ቢቀያየር …” ብለን ያንሹካሾክነው መረጃ ተረጋገጠ!
* ለጊዜው ቆንስል ጀኔራሉን ተክተው በጊዜያዊነት ቆንስል መስሪያ ቤቱን ለቀጣይ ሁለት ወራት የሚያስተዳድሩት በቆራጥ አመራራር ብቃታቸው የማይመሰገኑት ቆንስል ሸሪፍ  ከይሩ ናቸውም ተብሏል።
* ቆንስል ጀኔራል አቶ ዘነበ ከበደ ትናንት ምሽት ጉዳዩን ለማሳወቅ የኢህአዴግ ድርጅት  አባላት ስብሰባ ጠርተው እንደነበርና አብዛኛው አለመገኘታቸው ታውቋል። ድርጅት አባላት በተለይም ከጎናቸው የማይጠፉ የነበሩት ተጽዕኖ ፈጣሪ የህወሃት አባላት እንኳ አልተገኙም ተብሏል።
አቶ ዘነበ ከበደ በቆንስሉ ዙሪያ የህወሃት አባላትን አምባገነንነትን በማውረድና በማቀዝቀዝ፣ በሙስና፣ በድለላ፣ በማጭበርበር ስራ በቆንስሉ ዙሪያ የነበሩትን በማጥፋት እና በሌብነት አካባቢውን በማጽዳት ይታወቃሉ።
ህግ አዋቂ ሆነው በህግ ማዕቀፍ የመጡ ዜጎች ግፍ ሲፈጸምባቸው በመከላከሉ የረባ ስራ አልሰሩም የምላች  ሃላፊው ስልጣን ከተረከቡ ወዲህ ሶስት ከባባድ የህዝብ ማዕበል የተነሳባቸውን ፈተናዎች በጽናትና በቆራጥ አመራራቸው ድል ነስተው ማለፋቸውን አውቃለሁ።  ሃላፊው በአንጻሩ በመረጃ ልውውጥ የማያምኑ ፍትሃዊ በመሆኑ ሳይሆን በግላቸው ላመኑበት ጉዳይ ግንባራቸውን የሚሰጡ ኋላፊ ነበሩ።
አቶ ዘነበ ከበደ  በሳውዲ ከፍተኛ ሃላፊዎች ዘንድ ክብር የሚሰጣቸው በአማርኛም ሲናገሩ ወጋቸውን ለማስረዳት ተረት የሚያበዙ፣ ከዚህ በፊት ከነበሩት ኃላፊዎች እንግሊዝኛ አቀላጥፈው የሚናገሩ  አንደበተ ርቱዕ ግርማ ሞገስ ያላቸው፣ በአለባበሳቸው ጸዳ ያሉ ትክክለኛ የአንድ ሃገር ዲፕሎማት ክብርን የተጎናጸፉ ኃላፊ ነበሩ።
ከግማሽ ሚሊዮን የማያንሱ ኢትዮጵያውያን የኮንትራት ሰራተኞች ባለፉት ሶስትና አራት አመታት የገቡ ሲሆነ ኮንትራት ሰራተኞች ስለመጡበት ውል አቶ ዘነበ በጀርመን ራዲዮ ውይይት ፕሮግራም ተጠይቀው በኢትዮጵያና በሳውዲ በመንግስት መካከል የሁለትዮሽ የስራተኛ ልውውጥ ስምምነት አንደሌለ በግላጭ የነገሩን ኀላፊም ናቸው።
አቶ ዘነበ ከበደ ከዚህ በፊት በቆንስሉ ውስጥ የነበረውን የበከተ ቢሮክራሲና ኢ ፍትሃዊ አመራር በአደባባይ የተናገሩ ደፋርም ናቸው። ነዋሪው በግዳጅ ምንም የገንዘብ መዋጮ ሲጠይቁ ያልተሰሙ፣ ኮሚኒቲው ያልሆነ ምንገድ ሲሄድ እንደ በላይ ጠባቂነት ኢ ፍትሃዊ አካሔዱን እያዩ ሲያልፉም ታይተዋል። ለዚህ ተጠቃሹ ትምህርት ቤቱ በኮሚኒቲው ለከፋ አደጋ ሲዎድቅ የተመለከቱበት አካሔድ ሲሆን በመጨረሻው ሰአት ገብተው 120 ሽህ የሳውዲ ሪያል ከዝርፊያ አዳንኩ ብለው ቢነግሩንም  ዛሬ ድረስ የ3000 ታዳጊዎችና የ200 መምህራንና ሰራተኞች ያቀፈው መመኪያችን በጅዳ የኢትዮጵያውያን አለም አቀፍ ትምህርት ቤቱን ከአደጋ አላወጡትም። ያም ሆኖ ለትምህርት ቤቱ የተዝረከረከ አሰራር ምክንያትየየተባሉ አንዳንድ መሰረታዊ ለውጦችን ግን በቅርብ ተንቀሳቅሰው አምጥተዋል!
አቶ ዘነበ ከበደ እንደርሳቸው ጊዜያቸውን ሳይጨርሱ እንደ እርሳቸው ከስልጣን የተነሱትን አምባሳደር መርዋንን እና 12 አመት የጅዳን ቆንስል አንቀጥቅጠው የመሩት  የህወሃት ከፍተኛ ሰው አምባሳደር ተክለ አብ ከበደን አስተዳደር ብልሹ አካሔድ  ብቻ ሳይሆን የቆንስሉን ሰራተኞች በአደባባይ መመንቀፋቸው በኢህአዴግ የድርጅት አባላትና በሰራተኞች ዘንድ የተፈሩ ሲያደርጋቸው ለዛሬ ከስልጣናቸው መነሳትም የህወሃት አባላት ተጽዕኖ እንዳለበት ራሳቸው ህወሃቶች እየነገሩን ነው። ትናንት አንባሳደር መርዋንን ከስልጣን በማስነሳቱ ረዥም እጅ የነበራቸው ህዎሃትን ጨምሮ የተቀሩት የኢህአዲግ አባል ድርጅቶች ዛሬም በውጭ ጉዳ ከፍተኛ ሃላፊዎች ተጽዕኖ ፈጣሪነት በገሃድ ማሳያው ቀድምው የነገሩን እየደረሰ ማየት መጀመራችን ነው !  ዛሬም ማን ሊመጣ የሚችለው ሃላፊ የዲፕሎማሲያዊ እና የአስተዳደር ብቃት ሳይሆን አነጣጥሮ ተኳሽነቱና የዋለበትን የጦር አውድማ ድረስ በአድናቆት የህወሃት ካድሬዎች  ይነግሩን  ጀምረዋል።
ጉልቻ ቢቀያየር …
ከረፋድ እስከ ቀትር (ትናንት  ማክሰኞ መሆኑ ነው) አንዱ መረጃ ከተለያየ አቅጣጫ እዚህም እዚያም ደረሰኝ፣ በሹክሹክታ ስሰማው የሰነበትኩትን መረጃ እውነትነት ለማረጋገጥ ቢገደኝም የጭምጭምታውን አንድምታ ለማጣራት መሞከሬ አልቀረም። ብዙ ጣርኩ ግን ከመንግስት የቀረቡት ምንጮቸ እያወቁ “አናውቅም” ያሉኝ! ወደው ሳይሆን የእንጀራ ነገር ሆኖባቸው እንጅ አዲስ ነገር እንዳለ በከባቢው የሚታየው ድባብ ያሳብቃል … ይህን እያሰብኩ እያለሁ አንድ የማለዳ ወግ ርዕስ ከአፊ ገባ “ሳያልቅ የተጠናቀቀው ዘመቻና አልረጋ ያለው የጅዳ ቆንስል ወንበር …” ብየ ጀመርኩት … መቀጠል ግን አልቻልኩም!
በሰሞነኛው በባጀንበት የሳውዲ ኢትዮጵያውያን ክራሞት ዙሪያ የወገን እንግልት የሚያማቸው ወንድም አሉኝ። እኒሁ ከወደ ጅዳ ቆንስል መስሪያ ቤት ሁሌም መረጃ የሚያጋሩኝን ወዳጀን “ሹም ሽር ይደረጋል!” ተበሎ ሰምተው ያልተረጋገጠውን መረጃ ሲያቀብሉኝ “ስማው ብየ እንጅ ፣ እውነት እንኳ ሆኖ ወንበር ቢቀያየር ምን ዋጋ አለው፣ ለፖለቲካቸው የሚጠቅማቸውን እንጅ ለስደተኛው የሚፈይደውን አይልኩልን!” ነበር ያሉኝ … ” ጉልቻ ቢቀያየር ወጥ አያጣፍጥም !” እንዲሉ …
የሚፈለገው ሁሉ  ይሆናል … የሚያቆመው የለም! ለሁሉም አንድየ የሚበጀንን ይስጠን፣ ከሁሉም በላይ ለሃገራችን ምድር አብቅቶ በሰላም በፍቅርና በህብረት የምንኖርባት ሃገር፣ መድልኦ የማያውቅ፣ ሃገርና ህዝቡን የሚወድና ለዜጎቹ መብት የሚቆረቆር መንግስት ይሰጠን …ትናንት የሚፈለገው ሁሉ  ይሆናል… የሚያቆመው የለም ብለን ነበር የተለያየነው  ! አዎ  የሚፈለገው ሁኗል ፣ ይሆናል … የሚያቆመው የለም!…
“ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ይሾማል፣ የኢህአዴግ የድርጅት አባላትና ካድሬዎች ተጽዕኖ ፈጥረው በተናጠልና ተሰብስበው ያሽሩታል ፣ እንዲህ ተጉዘን የት እንደርስ ይሆን? “  ነበር ያሉኝ አንድ አልረጋ ያለውን የጅዳ ቆንስል ሹም ሽር ያስገረማቸው እህት …
እስኪ ቸር ያሰማን

Wednesday, February 12, 2014

Norway fundraising for Ethiopian migrant return back home from Saudi Arabia

Norway   fundraising for Ethiopian migrant return back home  from Saudi Arabia
prepared by Ethiopian community  in Norway from different society group take responsible to collect  money more than  140,000 Norwegian kroner
As you may be well aware, hundreds of thousands of Ethiopian migrants were displaced unjustly from Saudi Arabia in recent weeks. Although many of these migrants were returned to Ethiopia, several hundreds more are still scattered throughout the Middle East primarily in Saudi Arabia and Yemen. Almost all of these migrants including the ones returned to Ethiopia are suffering from lack of basic needs such as shelter, food, and closings. Many are unable to support themselves and their families.
It is to be remembered that Ethiopians all over the world were mobilized to defend the human rights of these Ethiopians and were able to stop the violence that was being committed on them. While the worldwide mass movement of Ethiopians to stand for the rights of our fellow Ethiopians was a remarkable act and was able to stop the violence, it is equally important to support these displaced people and their families by meeting their immediate needs and provide them with sustainable solutions towards making theme productive citizens in their homeland.
The Global Alliance for the rights of Ethiopians in Saudi Arabia (GAFRESA) was established by concerned patriotic Ethiopians around the world for this noble cause. The Global Alliance has been campaigning in various cities around the world to raise funds from Ethiopian communities and friends of Ethiopia’s. The Alliance has been working in collaboration with International Humanitarian Organizations such as the International Organization of Migrants (IOM) in order to reach out and help these displaced Ethiopians wherever they may be. So far the Alliance has raised over $60,000. This amount was donated to the IOM office in Washington DC in two installments of $30,000 and $32,000 in December 2013 and January 2014.
While this unprecedented act of humanitarian gesture by Ethiopians is encouraging, it is far too small compared to the level of support these hundreds of thousands of displaced Ethiopians need. The Alliance has continuing its effort to raise additional funds to be able to meet the dire needs of these Ethiopians.
In relation to this effort the Washington Metropolitan area network of the Global Alliance is planning to hold a fund raising event in Washington DC, scheduled for Sunday Feb. 16, 2014. The event is planned to draw participants from around the greater metropolitan area and possibly from the eastern coast of the USA.
We believe that it is of paramount importance for Ethiopians to stand together in times of our people’s sufferings. Every Ethiopian and friends of Ethiopia are cordially invited to come and participate at this event for a noble cause.
The event could also be an appropriate opportunity to deliver any funds raised by various groups in the Washington DC region for the purpose of supporting Saudi victims to the GAFRESA.
If you, for one reason or another can’t join the program, you can give a check or money order by calling a number provided below. Your contribution will be recognized at the event as well as a written confirmation will be mailed to your address.
Checks or money orders should be payable to “GLOBAL ALLIANCE FOR THE RIGHTS OF ETHIOPIANS”
If you have any questions, comments, or suggestions regarding this fund raising campaign, you can reach the organizers in any one of the following ways:
Via Email: dchapter2@gmail.com
By Telephone: (240) 821 0259
Website: www.defendethiopians.org

Tuesday, February 11, 2014

በኖርዌይ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ከ 100 ሺህ በላይ የኖርዌይ ክሮነር በሳውዲ ለተጎዱት ወገኖቻችን አዋጡ

በሳውዲ አረብያ በወገኖቻችን ላይ በደረሰው ጉዳት በመላው አለም የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ቁጣቸውን በሳውዲ ኢምባሲዎች ፊት ለፊት ሲገልፁ የነበረ መሆኑ ይታወሳል።ይህ ሁኔታ ከቁጭት ባለፈ በአለም አቀፍ ደረጃ ለተመሰረተው ''አለም አቀፍ ህብረት ለኢትዮጵያውያን መብት በሳውድ አረብያ'' (Global Alliance for the Rights of Ethiopians in Saudi Arabia) በኩል ለአለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት (International Organization for Migration - IOM) የሰበሰቡትን ገንዘብ ሰጥተዋል።ለምሳሌ ባለፈው ወር በአሜሪካ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ያሰባሰቡትን በድርጅቱ በኩል ለ አለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት (IOM) 30 ሺህ ዶላር አስረክበዋል። http://abbaymedia.com/2014/02/05/washington-dc-fundraising-for-ethiopian-migrants-displaced-from-saudi-arabia/  
ትናንት የካቲት 2፣2006 ዓም  በኦስሎ ከሳውዲ አረብያ ለተፈናቀሉ ወገኖቻችን መርጃ የሚሆን የገቢ ማሰባሰብያ መርሃ ግብር በኖርዌይ የኢትዮጵያ ማኅበረሰብ ተዘጋጅቶ ነበር። ማኅበርሰቡ ከተለያዩ የሕብረተሰቡ ክፍሎች በተውጣጡ ኮሚቴዎች አማካይነት ከትኬት ሽያጭ እና በኖርዌይ ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ከ100 ሺህ በላይ የኖርዌይ ክሮነር ( ከ 300 ሺህ ብር በላይ) ለማሰባሰብ ችሏል።

የትናንቱ የኦስሎ ዝግጅት የአለም አቀፉ የኢትዮጵያውያን እንቅስቃሴ አካል ሲሆን በመርሃ ግብሩ ላይ የአዲሲቷ ኢትዮጵያ ንቅናቄ ሊቀመንበር አቶ ኦባንግ ሜቶ እና ዝነኛዋ የመድረክ ሰው እና ጋዜጠኛ ገሊላ መኮንን ተገኝተዋል።

ገሊላ መኮንን የኢትዮጵያውያን እንቅስቃሴ እና ለወገን ደራሽነታቸው እጅግ የሚያስደስት መሆኑን ገልፃ በእዚሁ በጎ ተግባራቸው ጠንክረው እንዲቀጥሉ አሳስባለች።ቀጥላም  የሳውዲ አረብያውን ጉዳይ ኢትዮጵያውያን እንዲያውቁት ያደረገው የኢሳት አካል መሆኗ የሚያኮራት መሆኑን ስትገልፅ ከተሳታፊው ሞቅ ያለ ጭብጨባ ተቸሯታል።
 በዝግጅቱ ላይ የታደሙት ሌላው እንግዳ የአዲስቱ ኢትዮጵያ ንቅናቄ ሊቀመንበር አቶ ኦባንግ ሜቶ ነበሩ።አቶ ኦባንግ  ግልፅ እና ከልብ የመነጨ ሃገራዊ ፍቅር በምነበብበት ንግግራቸው ውስጥ ከተናገሩት የሚከተሉት ይገኙበታል-


''የኢትዮጵያ ሰንደቅ አላማ ሰው አልገደለም።ኢትዮጵያዊነት መከበር ያለበት ነው''
''እኛ ድሃ አይደለንም በተፈጥሮ ሀብት፣በውሃ በሁሉ ሃብታም ነን።ደንቆሮም አይደለንም ብዙ የተማሩ ሰዎች በመላው አለም አሉ…..ነፃነታችንን ተባብረን ማግኘት አለብን…ነፃነታችንን ከራሳችን መጀመር አለብን'' ካሉ በኃላ
በመጨረሻ እንዲህ አሉ '' እኛ ስንሰቃይ አሜሪካ ዝም ብላ ይሆናል፣የአውሮፓ ህብረት ምንም አላለ ይሆናል የኢትዮጵያ አምላክ ግን ከእኛ ጋር ነው ያለው''

በእዚህ ዝግጅት ላይ የኢህአዲግ/ወያኔን አንድ ለአምስት የመጠርነፍ ስታሊናዊ ተግባር የሚያሳይ ሙዚቃዊ ድራማ እና በሳውዲ አረብያ የሚኖሩ እህቶቻችንን ሕይወት የዳሰሰ ትረካን ጨምሮ ልዩ ልዩ ዝግጅቶች ቀርበዋል::
ጉዳያችን ጡመራ

Tuesday, February 4, 2014

ሰሞኑን የተለቀቀው የዘንድሮው የሂውማን ራይትስ ወች ሪፖርት የወያኔን አፈና በድጋሚ አጋለጠ


ወያኔ በሆድ አደር በለስልጣናቱ አማካኝነት እስኪሰለቸን በመደጋገም የተቃዋሚ
ፓርቲዎች ራእይ የለሽነትና ደካማነት እንጅ ሀገሪቱ ለፖለቲካ ጨዋታ ምቹ ናት፤
የሀገራችንን  ብርቅ  ነጻ  ጋዜጠኞች  ራሱ  ሽብርተኛ  እያለ  ለሚጠራቸው  ፖለቲካ
ድርጅቶች ይወግናሉ፤  ወይም ደግሞ የሽብርተኛ ድርጅቶች ጉዳይ አስፈጻሚዎች
ናቸውና የመሳሰሉትን እየደረደረ የኢትዮጵያን ሕዝብ ሲዋሽና ዓለምን ሲያታልል
ቢከርምም  እንሆ  ዓለማቀፍ  እውቅና  ባላቸው  ድርጅቶች  ሪፖርት  በተደጋጋሚ
እየተጋለጠ መሆኑ እየታየ ነው።
ሰሞኑን  የወጣው  የ2013ን  እንቅስቃሴ  የሚገመግመው  የሂውማን  ራይትስ  ወች
ሪፖርት  እንደሚያመለክተው  ግን  ፋሽስት  ወያኔ  ለራሱ  ህልውና  ይጠቅመው
ዘንድ  የፖለቲካ  ምህዳሩን  በማትበብ  ማንም  ግለሰብም  ሆነ  ፖለቲካ  ፓርቲ
ሊነቀሳቀስ  ከማይችልበት  ደረጃ  ላይ  እንዳደረሰው  አጋልጧል።  ይህ  የድርጅቱ
ሪፖርት  የነጻ  ሚዲያ  ህልውና  በኢትዮጵያ  ከፍተኛ  አደጋ  ውስጥ  እንደወደቀ
ጨምሮ አጋልጧል።

ከጥቂት አመታት በፊት ፋሽስት ወያኔ ባጸደቀው የጸረ ሽብርተኝነት አዋጅ የተነሳ
ፖለቲከኞችና  ጋዜጠኞች  ሽብርተኛ  ተብለው  እንደታሠሩና  እንደተፈረደባቸው
የጠቀሰው  የተቋሙ  ሪፖርት  በህጋዊና  ሰላማዊ  መንገድ  የሚንቀሳቀሱ  የፖለቲካ
ፓርቲዎች  በፍርሃት  ቆፈን  ውስጥ  እንዲቀመጡ  ተደርገዋል  ብሏል።  ከዚህ
በተጨማሪም  ሌሎች  የሰብዓዊ  መብት  ጥሰቶችም  ከልክ  በላይ  እየተባባሱ
መምጣታቸውን  የጠቀሰው  ሪፖርት  ህጋዊ  ታራሚዎች  በተለይም  ጋዜተኞችና
ፖለቲካ  እስረኞች  በገለልተና  አካላት  እንዴይጎበኙ  እገዳ  ይታልባቸዋል  ሲል
አጋልጧል።