Monday, December 4, 2017

በኢትዮጵያ የፖለቲካ ጉዳዮች ላይ ለመነጋገር የአሜሪካ ልዑክ ወደ አዲስ አበባ አቀኑ

ዋዜማ ራዲዮ- ላለፉት ሁለት ዓመታት ቀውስ ያልተለየውን የኢትዮጵያ የፖለቲካ ሁኔታ አንስቶ ለመነጋገር የአሜሪካ ከፍተኛ ልዑክ ወደ አዲስ አበባ እንደሚጓዝ የአሜሪካ የውጪ ጉዳይ መስሪያ ቤት አመለከተ።የአሜሪካ የውጪ ጉዳይ መስሪያ ቤት የአፍሪቃ ጉዳዮች ተጠባባቂ ረዳት ሀላፊ ዶናልድ ያማማቶ ከወራት በፊት ከኢትዮጵያ መንግስት ባለስልጣናት ጋር መግባባት የተደረሰባቸው የፖለቲካ ማሻሻያዎች ባለመተግበራቸው የአሜሪካ መንግስትን ቅሬታ ያስረዳሉ ተብሎ ይጠበቃል።
የፖለቲካ እስረኞችን መፍታት ፣ የሰብዓዊ መብት አያያዝን ማሻሻልና ሁሉንም የፖለቲካ ሀይሎችን ያሳተፈ ውይይት መጀመር እንዲቻል ቀደም ሲል በአዲስ አበባ በሚገኙ ዲፕሎማቶችና በመንግስት ባለስልጣናት በኩል በዝግ ውይይቶች መካሄዳቸውን ለጉዳዩ ቅርብ የሆኑ የዋዜማ ምንጮች ይናገራሉ።
በቅርቡም የአሜሪካ ኦክላህማ ግዛት ሴናተር ጂም ኢንሆ ጠቅላይ ሚንስትር ሀይለማርያም ደሳለኝንና የክልል ፕሬዝዳንቶችን ጨምሮ በሀገሪቱ ባለው የፖለቲካ ቀውስ ዙሪያ ሰፊ ምክክር ማድረጋቸው ይታወሳል።

አሁን ዶናልድ ያማማቶ የሚያደርጉት ጉብኝት በተለይ በገዥው ፓርቲ ውስጥ የተፈጠረው አለመግባባት በቶሎ እልባት እንዲያገኝና ከዚህ ቀደም የቀረቡ የፖለቲካ ማሻሻያዎች እንዲተገበሩ ለማበረታታት ነው ተብሏል።
ያማማቶ በ 1997 ዓ.ም ምርጫ ወቅት የተቃዋሚ ፓርቲ ተወካዮችን ከገዥው ፓርቲ ጋር በዝግ በማወያየት ፖለቲካዊ መፍትሄ ሲያፈላልጉ የነበሩ ዲፕሎማት ናቸው።
በጣም ምስጢረኛ ናቸው የሚባሉት ያማማቶ በአሜሪካ አስተዳደር ውስጥ በተለይ የምስራቅ አፍሪቃን ጉዳይ በጥልቀት የመረዳትና መፍትሄ የመጠቆም ብቃት እንዳላቸው ይነገርላቸዋል።
በዚህ ጉብኝታቸው በፀረ ሽብር ትብብር ጉዳዮችና በሌሎችም አጀንዳዎች ላይ ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር ውይይት ያደርጋሉ።
በቀጣዩ ወር መጨረሻ ላይ የአፍሪቃ ህብረት ሊቀመንበርነቱን ከሚረከቡት የሩዋንዳው ፕሬዝዳንት ፖል ካጋሜ ጋር በኪጋሊ ቆይታ የሚያደርጉ ሲሆን በኬንያና ሶማሊያም አጭር ቆይታ በማድረግ በፀጥታ ጉዳዮች ላይ ለመነጋገር ዕቅድ እንዳላቸው ዋዜማ ያገኘችው መረጃ ያመለክታል።
by satenaw
BBC Amharic News

Thursday, August 17, 2017

ሕዝባዊ ትግሉና ዲያስፖራው

ሕዝባዊ ትግል ወይም አመጽ ወሳኝ የትግል ስልት መሆን እንደሚችል ካለፉት ጥቂት ዓመታት ጀምሮ ኢትዮጵያውያን እያካሄዱት ያሉት ትግል ጥሩ ማስረጃ ነው። ትግሉ እስካሁን ድረስ ከተገመተው በላይ በርካታ ድሎችን አስገኝቷል። ቀጥለው የተዘረዘሩትን ዋና ዋና ክስተቶች  የትግሉ ውጤት እንደሆኑ መናገር ይቻላል። አንደኛ መንግስት ሊተገብራቸው ያቀዳቸውን ፕሮጀክቶች ለጊዜውም ቢሆን በሕዝብ ትግል የተነሳ እንዲቆሙ አድርጓል። ሁለተኛ ትግሉ አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ እንዲታወጅ አድርጓል። ሦስተኛ የክልል ባለ ሥልጣናት በተወሰነ መልኩ ሕወሓትን እንዲገዳደሩ የሞራል ተነሳሽነት ሰጥቷል። 


አራተኛ ከፍተኛ የፌዴራል የመንግስት ባለ ሥልጣናት ከምንም ጊዜ በላይ እርስ በእርስ እንዳይተማመኑ አድርጓል። አምስተኛ ውጥረቱን ለማስተንፈስ  በሚመስል መልኩ መካከለኛና ዝቅተኛ ባለ ሥልጣናትና ካድሬዎች ከሥራ እንዲባረሩ ትግሉ ምክንያት ሆኗል። ብዙዎችም በስርቆት ክስ ዘብጥያ እንዲወርዱ ምክንያት ሆኗል። ስድስተኛ አገዛዙ ከሕዝብ ሊሰበስበው የነበረው የገቢ ግብር በታቀደው መሠረት እንዳይሰበሰብ አድርጓል። ሰባተኛ ሕዝባዊ ትግሉን ለመግታትና ለማቆም  መንግስት በወሰደው አረመናዊ ጭፍጨፋ የተነሳ እርዳታ የሚለግሱት የውጭ አካላት የአገዛዙን ማንነት ይበልጥ እንዲረዱ ፖሊሲያቸውንም እንደገና እንዲፈትሹ አድርጓል። ስምንተኛ ምንም እንኳን ከፍተኛ የሕይወት መስዋዕትነት ቢከፈልበትም ሕዝብ በእምቢታው ከቀጠለ መንግስትን ማንበርከክ እንደሚችል የማይረሳ ትምህርትና ተሞክሮ ተገኝቷል። ለዚህም ነው በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ጌዜ እንኳ ሳይቀር ትግሉ ሊቀጥል የቻለው! በመሆኑም እስካሁን ድረስ የተካሄደው ትግል እጅግ በብዙ መልኩ ውጤታማ እንደሆነ መንግስት ሳይቀር ሊቀበለው የሚገባ ሐቅ ነው።              

ዳሩ ግን ትግሉ ፖለቲካዊ ሥርዓቱ ሥር ነቀል ለውጥ እንዲያደርግ ወይም መንግስት ሙሉ በሙሉ  ሥልጣኑን ለሕዝብ እንዲያስረክብ አላደረገውም። ለዚህም በርካታ ምክንያቶች ሊጠቀሱ ይችላሉ። አንደኛ ትግሉ በፈረቃ መካሄዱ  መንግስት ኃይሉን እያጠናከረ ሕዝቡን እንዲደፍቅ እድል ፈጥሮለታል። የሙስሊሞች ትግል፣ በኦሮሚያ የሚካሄደው ትግል ከዚያም የአማራው ትግል በሂደትና በተለያዩ ጊዜያት የመጡና ያልተቀናጁ ናቸው። አሁንም ቢሆን አመጹ በተለያዩ አካባቢዎች በተለያዩ ጊዜያት እየተካሄደ ይገኛል። ይህ ፈረቃዊ ትግል የመንግስት ወታደሮች ከቦታ ቦታ እየተስፈነጠሩ እንዲመቱት አስችሏል። ሁለተኛ ትግሉ በፈረቃና ያለ ቅንጅት  የሚካሄደው ወጥ አመራር ስለሌለው ነው። ትግል  መሪን ይወልዳል እንዲሉ በሂደቱ ከፊት የተሰለፉ  ጀግኖች ብቅ ብለው ነበር። ይሁንና ሳይውሉ ሳያድሩ ምህረት የሌለው የካድሬ በትር አርፎባቸዋል። ብዙዎች በመንግስት ኃይሎች ተገድለዋል፣ ታስረዋል፣ ተሰደዋል፣ በሽተኞች ተደርገዋል። ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ ተቃዋሚ ፓርቲዎችም ወገባቸውን ተመተው በመኖርና ባለመኖር መካከል እያጣጣሩ ይገኛሉ። ይህን ሁሉ በማድረግ ግን መንግስት ውጤታማ እንደሆነ መናገር ይቻላል! ሦስተኛ በቂና የተቀናጀ  ደጀንና ድጋፍ የለም። ትግሉን የሚያካሂደው ሕዝብ እርሻውንና ንግዱን ትምህርቱንም ትቶ በራሱና በቤተሰቡ የዕለት ተዕለት ኑሮ ፈርዶ  ነው። ይህ አይነት ትግል ፍጥነትና ዘለቄታዊ ውጤት የሚያመጣው ሁለንተናዊ ድጋፍ ሲኖር ነው። ይህም ሁሉ ሆኖ ትግሉ መቀጠሉ የሕዝቡን የብሶት መጠን ከማሳየቱም በላይ ሕዝብና መንግስት ዳግም ላይገናኙ በይፋ ፍቺ መፈጸማቸውን ያበስራል።    
             
የዲያስፖራው እንቅስቃሴ

ኢትዮጵያዊው ዲያስፖራ (በውጭው ዓለም ያሉ ኢትዮጵያዊ የፖለቲካና የሲቪክ ተቋማት፣ የመገናኛ ብዙኃንና  ግለሰቦች) በበኩሉ አገር ቤት ትግሉ በሚካሄድበት ወቅት የራሱን አስተዋጽዖዎች ሲያደርግ ቆይቷል። ቀጥለው የተዘረዘሩት ጎላ ብለው የታዩ እንቅስቃሴዎች ተካሂደዋል። ይህ ማለት ግን እነዚህ እንቅስቃሴዎች በሕዝባዊ ትግሉ አማካኝነት የተከናወኑ ናቸው ማለት አይደለም። ትግሉ በሚካሄድበት ወቅት አብረው በመከሰታቸው ከትግሉ እንቅስቃሴ ጋር ቢወሱ ክፋት የለውም። እንዲያውም በርካታ እንቅስቃሴዎች ትግሉን በተለያዩ  መንገዶች ለመደገፍ ያለሙ ናቸው። 
  • በረሃ ያሉ የትጥቅ ትግሎች ከበፊቱ የተለየ እንቅስቃሴ አድርገዋል። እንደ ድርጅቶቹ መግለጫዎች ከሆነ አርበኞች ግንቦት 7 እና የአማራ ዴሞክራሲያዊ ኃይል ንቅናቄ ወታደሮቻቸውን ከኤርትራ ወደ ኢትዮጵያ ለማስገባት ችለዋል። እንዲያውም ከአገዛዙ ኃይሎችና መገለጫዎች ጋር ፍልሚያ እንደጀመሩም  አሳውቀዋል። ይህ በራሱ በቀጣይነት ለሚደረግ ትግል ወሳኝ ስለሆነ በራሱ እንደ ድል ሊቆጠር ይችላል። አገር ቤት ሆኖ ለሚታገለው ሕዝብም ሞራልና ተስፋ ሊሆን ይችላል
  • ምንም እንኳን የድርጅቶቹ አቅምና ቁመና ገና በግልጽ ባይታወቅም አራት ድርጅቶችን ያቀፈው የኢትዮጵያ አገራዊ ንቅናቄ ምስረታም አንድ እርምጃ  ነው። ብሄራዊ አደረጃጀትንና አጀንዳን ሊያጠናክር ይችላል 
  • በቪዥን ኢትዮጵያ አነሳሽነት ዕውቀትና ጥበብ የፈሰሰባቸው ታላላቅ ኢትዮጵያ አቀፍ ጉባኤዎች ተካሂደዋል። ለብሄራዊ እርቅና መግባባት እንዲሁም ባጠቃላይ ለፖሊሲ ግብዓት የሚሆኑ መረጃዎች ተሰብስበዋል። የበለጠ መተዋወቅ እንዲኖር ከማስቻሉም በላይ በጋራ የጋራ ብሄራዊ የፖሊሲ አቅጣጫዎችን መለየት እንደሚቻል ትምህርት አስተላልፏል
  • 17 አባላት ያሉት የኢትዮጵያ ብሄራዊ አንድነት ጉባኤ ተመስርቷል። እንደ ጉባኤው የአቋም መግለጫ ከሆነ ይህ ኮሚቴ «የሽግግር ሂደት ሊመራ የሚችል፤ ሁሉን አሳታፊ የሆነ ብሔራዊ ምክርቤት በአጭር ጊዜ ለመመሥረት የሚያስችል ጥናት የሚያደርግ፤ ከሌሎች ተመሳሳይ ጥረት ከሚያደርጉ ወገኖች ጋር በቅንጅት የሚሰራና የኢትዮጵያ ብሔራዊ አንድነት ጉባኤ ቀጣይነት ባለው መልኩ በየዓመቱ በተለያዩ ከተሞች እንዲደረግ” ያስተባብራል። ይህም በራሱ መልካም ጅምር ነው
  • የኦሮሞውን ማኅበረሰብ በማስተባበርና በማደራጀት በኩል የኦሮሞ ሚዲያ ኔትዎክ ከፍተኛ የሚባል ሥራ አከናውኗል። በኦሮሚያ አካባቢዎች የተካሄዱትን ትግሎች ለዓለም አስተላልፏል።  የመንግስትን ብልሹ አሠራሮች አጋልጧል
  • የአማራውን ማኅበረሰብ ለመታደግ ደግሞ በአጭር ጊዜ እንደ እንጉዳይ የፈነዱ ንቅናቄዎች ድርጅቶች ተፈጥረዋል። ምንም እንኳን እርስ  በርሳቸው መናበብ ባይችሉም የተለያዩ እንቅስቃሴዎችን እያደረጉ ይገኛሉ። ዳሩ ግን የአማራው መደራጀት እንደ ሌሎች ብሄር ተኮር ድርጅቶች በቀላሉ ተቀብሎት ባለማግኘቱ ቀላል የማይባል ክርክርና ውይይት ተካሂዷል
  • ኢትዮጵያ ተኮር ድረ ገጾችም ዜናዎችን ከመዘገብ በተጨማሪ ውይይቶችን በማነሳሳትና በማሰራጨት ከፍተኛ አስተዋጽዖ አድርገዋል   
  •  ምናልባትም ከነዚህ ሁሉ እንቅስቃሴዎች እጅግ በላቀ ደረጃ ትግል ያደረገ ተቋም ቢኖር ኢሳት ነው። የአገር ቤቱን ትግል በትኩሱ ከመዘገቡም በላይ ምሁራንንና የተቋማት አመራሮችን እንዲሁም ግለሰቦችን በመጋበዝ ታሪካዊ ሥራ አከናውኗል። ኢትዮጵያዊያን መንግስት የሚያደርሰውን አድሎ፣ ሙስናና ዘረኝነት በተጨባጭ እንዲገነዙ አድርጓል። ለመንግስት ከፍተኛ የራስ ምታት ሆኖበታል። ኢሳትን ለማፈን በሚሊዮን የሚቆጠር ዶላር አውጥቷል። ላለማጋነን ከሁሉም የዲያስፖራ ትግሎች መንግስትን በእጅጉ ያሸበረውና የተገዳደረው ኢሳት ነው!    
ከዚህ ባለፈ በውጭው ዓለም የሚኖረው ኢትዮጵያዊ ማኅበረሰብ የተበታተኑ የገንዘብ፣ የሞራልና የዲፕሎማሲ ድጋፎችንም ለማቅረብ ሞክሯል። ባጠቃላይ ሲታይ ግን ከኢሳትና ከሌሎች ሚዲያዎች  በስተቀር ዲያስፖራው ለሕዝባዊ ትግሉ በቀጥታ ያበረከተው አስተዋጽዖ እምብዛም አይደለም። እንዲያውም ምስኪን ኢትዮጵያዊያን በየቀኑ መስዋዕት እየሆኑ በዲያስፖራው የሚካሄዱት አንዳንድ ውይይቶችና ክርክሮች ለትግሉ የማይረባ ከመሆናቸውም በላይ አገር ቤት ያለውን ኢትዮጵያዊ ግራ አጋብቷል ለማለት ይቻላል።  ዲያስፖራው ካለው ምቹ ሁኔታ አኳያ ሊያደርገው የሚገባውን  አላደረገም።   

የዲያስፖራው ፈተናዎች

ዲያስፖራው እጅግ ብዙ ፖለቲካዊና ሲቪክ ተቋማት እያሉት ለምንድን ነው የተቀናጀና ትርጉም ያለው ድጋፍ ሳያደርግ የቀረው? በርካታ ቀጥታዊና ኢ-ቀጥታዊ ምክንያቶችን መዘርዘር ይቻላል።  
  • የተወሰኑት ድርጅት እንደሆኑ ቢናገሩም ገና የድርጅት አቅምና ባህርይ የላቸውም። በማኀበራዊ መገናኛ ብዙኃን ገዝፈው ቢታዩም መሬት የነካ እንቅስቃሴ የላቸውም! የጥቂት ግለሰቦች ብቻ  መድረክ የሆኑ አሉ
  • በዲያስፖራው ስም ተቃዋሚ እንደሆኑ ቢናገሩም ተቃዋሚ ያልሆኑም አሉ። እንዲያውም የዲያስፖራውን ትግል የሚያቀጭጩ በስውርም መረጃ ለመንግስት የሚቀልቡ እንዳሉ ይታመናል
  • ቀላል ቁጥር የሌላቸው ድርጅቶች ደግሞ በአንድ ወቅት ካዘጋጁት የድርጅታቸው መርሐ ግብር ውጭ ሌላ አማራጭ እንዳለ አይቀበሉም። የትግል ግብና ዓላማ ስልት ሳይቀር እነሱ ካስቀመጡት የተለየ ከሆነ ለትብብር በራቸው ዝግ ነው። ይህም አልፎ ሌሎችንም ለማደናቀፍ በተለያዩ መንገዶች የሚንቀሳቀሱ ይኖራሉ
  • ሰላማዊና ሁለ ገብ የትግል ስልቶችን  የመረጡት ድርጅቶች የትጥቅ ስልትን ከመረጡ ድርጅቶች ጋር ለመናበብና ለመሥራት አይፈልጉም። በሽብርተኝነት እንዳይፈረጁም ይሰጋሉ! እንዲሁም  ቋንቋንና ዘርን መሠረት ያደረገና ብሄራዊ አስተሳሰብን መነሻው ያደረገ አደረጃጀት ለትብብር ቀርቶ ለሰከነ ውይይትም አላበቃም። አገር ቤት የንጹሃን ደም በየቀኑ በወታደር እየፈሰሰ ዲያስፖራው የሚከራከረው በዘር ስለመደራጀትና አለመደራጀት ነበር። አንዱ ሌላውን በተቃርኖ አስቀምጦታል
  • የግል አጀንዳ ወይም ጥቅም ይዘው የሚንቀሳቀሱ አባላት እንደሌሉ ማሰብም የዋህነት ነው
  • የአባላት የአቅም ሁኔታም ሌላው እንቅፋት ነው! ሕዝባቸውን ለማገልገል ፍላጎት ቢኖራቸውም እንዴት መንቀሳቀስና መተባበር እንዳለባቸው ብዙም የማይረዱ አሉ። ስሜት እንጅ አቅም የሌላቸው የድርጅት ሓላፊዎች፣ ጸሐፊዎችና ግንኙነት  ክፍሎችን ማየት አዲስ ጉዳይ አይደለም
  • ዕውቀቱና ተሞክሮው ያላቸው ደግሞ ለትናንት ታሪካቸው እስረኛ ሆነው ይስተዋላሉ። በጃንሆይና በደርግ በኋላም በወያኔ ዘመናት በተለያይ የፖለቲካ ትግሎች የሚተዋወቁ አብዝተውም የሚተቻቹ ሞልተዋል። እነዚህ ሰዎች አይደለም አብረው ሊሠሩ አንዱ ሌላውን ጥሎ ለመሄድ ብዙም አይገዳቸውም
  • አብዛኛው ዲያስፖራ ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ የሚያካሂደው በትርፍ ጊዜ ነው። አድካሚ ከሆነ ሙሉ ሥራና ከቤተሰብ የተረፈ ቅንጭብጫቢ ጊዜ ነው ለፖለቲካ ሥራ የሚመደበው! ይህ ደግሞ  እጅግ የታሰበበት አዋጭ ሥራ እንዳይታቀድና እንዳይከናወን እያደረገ ነው  
  • ብዙ ሊባሉ የሚችሉ የድርጅት አመራሮች በዝምድናና በትውውቅ የተሳሰሩ ናቸው። ይህም ከራሳቸው ምቹና ስጋት የሌለው ከሚመስል አሠራር ወጥተው ከሌሎች ጋር አጥጋቢ ትብብርን እንዳያደርጉ ያደርጋል። ይህ አሠራር ለግልጽነትና ተጠያቂነትም አይመችም  
  • ዲያስፖራው በሃይማኖት ተቋማት ሳይቀር የተከፋፈለ ነው። ሃይማኖትን ሽፋን በማድረግ በስውርና በይፋ መንግስትን የሚደግፉ አሉ። እንዲሁም ኢትዮጵያ ውስጥ ባለው ሲኖዶስ ስር ያለ ቤተ ክርስቲያንና ክርስቲያን ሁሉ የወያኔ፣ ውጭ ባለው ሲኖዶስ ስር ያሉ ሁሉ ደግሞ የተቃዋሚ ጎራ ተደርገው ይታያሉ። ይህ ሾላ በድፍን የሆነ አስተሳሰብ አንድነትና መናበብ እንዳይኖር የራሱን አስተዋጽዖ አድርጓል
  • ብዙ ድርጅቶች ውሳኔ አሰጣጣቸው እንደ ቀድሞው አሠራር ከላይ ወደ ታች  ነው። ከፍተኛ አመራሮች በራቸውን ዘግተው ይወስናሉ።  መካከለኛና ዝቅተኛ አማራሮች እንዲሁም አባላት ደግሞ  ውሳኔችን የመፈጸም የውዴታ ግዴታ አለባቸው። በሕዝባዊ ውይይት ስም ጉባኤ ተጠርቶ መግለጫና ማስታወቂያ ብቻ አሰምቶ መሄድ የተለመደ ነው። ይህ አይነት የሥራ ባህል አባላት የባለቤትነት ስሜትና የሥራ መነቃቃት እንዳይኖራቸው ከማድረጉም በላይ ያላቸውን አማራጭ ተሞክሮዎች  በውይይት አዳብረው እንዳይጠቀሙ ይገድባል። በቆይታም እቅዶች በአግባቡ ሳይፈጸሙ ይቀራሉ። ይህም በአባላት ዘንድ መሰላቸትና ከትግል መራቅን ያስከትላል                      
በአጠቃላይ ሲታይ ዲያስፖራው ካለው እምቅ አቅም አኳያ ሲታይ ለሕዝባዊው ትግሉ እምብዛም ድጋፍና ደጀን ሊሆን አልቻለም። ሁኔታዎች በዚህ የሚቀጥሉ ከሆነም በዲያስፖራውና አገር ቤት ባለው ኢትዮጵያዊ መካከል ያለው የሥራ ግንኙነት ፈጽሞ ሊቋረጥ ይችላል። በመሆኑም ዲያስፖራው ሰከን ብሎ ለመራመድ ይችል ዘንድ አሠራሩንና  ግቡን መፈተሽ ይኖርበታል። ለግል ጥቅምና ዝና የሚቋምጡ፣ የዲያስፖራውን ትግል በተለያዩ መንገዶች ከውስጥ ሆነው የሚያቀዘቅዙ፣ ግልጽነትና ተጠያቂነትን የሚፈሩ፣ በ60ዎቹና በ70ዎቹ ታሪክና ፖለቲካ የሚቆዝሙ፣ ባጠቃላይ ወቅታዊና የዴሞክራሲያዊ አሠራር ባህል የማይዋጥላቸውን ከአመራር ቦታዎች ሊነሱ ይገባል። በአንጻሩም የራሳቸውን ድርጅት ብቻ በማፍቀር ሌሎችን የሚቃወሙ መንግስትን ካልሆነ በስተቀር ማንንም እየጠቀሙ እንዳልሆነ ይረዱ። በትውውቅ በዘፈቀደና በስሜት የሚደረግ ሥራ መቆም ይኖርበታል። ልዩነትን አቻችሎ መናበብን ከዚያም መተባበርን መልመድ ከምን ጊዜውም በላይ አሁን ያስፈልጋል።  

ማጠቃለያ

ዲያስፖራው ከላይ የተዘረዘሩት ተግዳሮቶች ቢኖሩበትም በአገሩ ጉዳይ ከማሰብና ከመጨነቅ ብሎም የሚቻለውን ከማድረግ አልቦዘነም። ለዚህም ምስጋናና እውቅና ያስፈልጋል! ይሁንና ውጤት ለማምጣት  ከተፈለገ ትግሉ በብዛትም በጥራትም ተጠናክሮ ሊመራ ያስፈልገዋል። የተናጥል እንቅስቃሴዎች የትም አያደርሱንምና ቅንጅትና መናበብ ያስፈልጋል። 


እስካሁን ድረስ እንደታዘብነው ከሆነ የፖለቲካ ፓርቲዎችና የሲቪክ ተቋማት ፍጹም ውህደት እንዲፈጥሩ መጠበቅ የሚከብድ ይመስላል። ያለው ብቸኛ አማራጭ እያንዳንዱ ድርጅት የራሱን ምንነትና ማንነት እንደያዘ የጋራ ፕሮጀክቶችን መንደፍ ነው። ይህም ማለት ድርጅቶች ስማቸውንና የራሳቸውን ፕሮግራም እንደያዙ በጋራ ሊሠሯቸው የሚገቡ ጉዳዮችን አብሮ መለየትና መሥራት ነው። ሁሉም ድርጅት ባይቻል አብዛኛው ተገናኝቶ  መወያየትና ሁሉንም የሚወክል አስተባባሪ ግብረ ኃይል ማቋቋም ወሳኝ ነው። ከዚህ በፊት የተመሰረቱት አገራዊ ማለትም ብሄራዊ ንቅናቄዎች ይበልጥ ግልጽነትን፣ ሁሉን አሳታፊነትንና ተጠያቂነትንም አዳብረው ሊወጡት የሚችሉት ታላቅ ሓላፊነት ነው። ያለበለዚያ በተናጥል የሚደረግ ትግል ተሳተፍን ለማለት ካልሆነ በስተቀር ለምስኪኑ የኢትዮጵያ ሕዝብ የሚፈይደው ጉዳይ አይኖርም። 
          
በዶክተር ተክሉ አባተ

Thursday, July 27, 2017

በአዲስ አበባ ታትሞ የሚወጣው ሰንደቅ ጋዜጣ እንደዘገበውና ዜና አቅራቢው ፋኑኤል ክንፉ እንዳጠናቀረው  በሙስና ወንጀል የተጠረጠሩ 34 ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ባለሀብቶችና ደላሎች፤ በትላንትናው ዕለት በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የኢፌዴሪ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት አስታወቀ::
የጽ/ቤቱ ኃላፊ ሚኒስትር ዶ/ር ነገሪ ሌንጮ ትላንት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፣ 34 የሚሆኑ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት፣ ባለሀብቶችና ደላሎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን አስታውቀዋል፡፡ ኃላፊዎቹ ተጠርጥረው የተያዙት “በፖሊስ፣ ዐቃቤ ህግና በፌደራልና አዲስ አበባ ዋና ኦዲተር መ/ቤቶች በተደረገ የማጣራት ስራ የሙስና ተግባር ውስጥ ተሳትፈው በመገኘታቸው መንግስት ሙስናን ለመከላከል በያዘው ቁርጠኛ አቋም ነው፤” ሲሉ ሚኒስትሩ ተናግረዋል::
በሙስና ወንጀል የተጠረጠሩ  ኃላፊዎች ከተገኙባቸው የመንግስት  ተቋማት መካከል፤ የፌደራል መንገዶች ባለስልጣን፣ የአዲስ አበባ መንገዶች ባለስልጣን፣ ስኳር ኮርፖሬሽን እና የገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ሚኒስቴር መስሪያቤቶች ጋር ይገኙበታል፡፡
የሰንደቅ ምንጮች እንደገለጽት፣ በስኳር ኮርፖሬሽ በኩል ተጠርጥረው ከተያዙ መካከል  የቀድሞው የተንዳሆ ስኳር ፋብሪካ ዋና ሥራ አስኪያጅ የነበሩት አቶ አበበ ተስፋዬ እና የቀድሞው የተንዳሆ የፋይናንስ ሥራ አስኪያጅ የነበሩት አቶ ተስፋዬ ድምፁ እንደሚገኙበት ታውቋል፡፡ እንዲሁም፣ አቶ በኃይሉ ገበየሁ የኮርፖሬሽኑ ንብረት አስተዳደር ዳሬክተር እና አቶ ኤፍሬም አለማየሁ የቀድሞ የኮርፖሬሽኑ፣ ግዢና ንብረት አስተዳደር ዘርፍ ምክትል ዳሬክተር ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡
የመተሐራ ስኳር ፋብሪካ ግዢ ቢሮ ኃላፊ አቶ እንዳልካቸው ግርማ፤ እንዲሁም ወ/ሮ ሠናይት ወርቁ እና አቶ ኃየሎም ከበደ ተጠርጥረው በቁጥጥር ሥር ማዋላቸው ታውቋል፡፡
አንድ የቀድሞ ሚኒስትር እና አንድ ሚኒስትር ዴኤታም ተጠርጥረው በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን ምንጮቻች የጠቆሙን ቢሆንም፣ ከሚመለከታቸው አካላት ለማረጋገጥ አልቻልንም፡

Sunday, June 18, 2017

አገራዊ ንቅናቄው የአገራችንን የፖለቲካ ችግር የሚመጥን መፍትሄ ለመፈለግ ጠቃሚ ነው - ፕ/ብርሃኑ ነጋ።የኢትዮጵያ ጉዳይ ከልብ ያሳስበኛል - አቶ ሌንጮ ለታ

ሰኔ 10፣2009 ዓም 

==============
የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት በኖርዌይ ቅዳሜ ሰኔ 10፣2009 ዓም በኦስሎ፣ኖርዌይ የኢትዮጵያ አገራዊ ንቅናቄ ጉባኤ ሁለት ከፍተኛ ኃላፊዎችን ጋብዞ ጉባኤ አካሂዶ ነበር።ይሄው በኦስሎ የቀይ መስቀል ዋና መስርያ ቤት አዳራሽ የተካሄደው ጉባኤ ላይ ከ200 ሰው በላይ የታደመበት ነበር።በጉባኤው ላይ የተጋበዙት የአርበኞች ግንቦት 7 ሊቀመንበር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና የኦሮሞ ዲሞክራሲያዊ ግንባር ሊቀመንበር አቶ ሌንጮ ለታ ነበሩ።
የዝግጅቱን መክፈቻ የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት በኖርዌይ ሰብሳቢ አቶ ይበልጣል ጋሹ በንግግር ከተከፈተ በኃላ  የመጀመርያ ተናጋሪ የነበሩት አቶ ሌንጮ ለታ ነበሩ።
አቶ ሌንጮ "ተቀምጨ እንዳልናገር አጭር ነኝ" በሚል ቀልድ አዘል ንግግር ተሰብሳቢውን ፈገግ ካስደረጉ በኃላ የመተባበር አስፈላጊነት ላይ አፅኖት ሰጥተው ተናግረዋል።በመቀጠልም " በ1966 ዓም ንጉሱ ከስልጣን ሲወርዱ እርሳቸው ይወረዱ እንጂ መጪው ጊዜ የተሻለ እንደሆነ በጣም ተስፋ አድርገን ነበር። ካሉ በኃላ ሆኖም ግን ደርግ መጣ ብለዋል።
አቶ ሌንጮ አያይዘውም ደርግ ሲመጣ ከደርግ የባሰ ሊመጣ አይችልም ብለን ስናስብ የባሰ መጣ።ሆኖም ግን ማሰብ የሚገባን ደርግ ሲገድል በቀጥታ `የፍየል ወጠጤ` እያለ ነበር።ስለሆነም የገደለውን ቁጥር መገመት ይቻላል።የአሁኖቹ ግን በስውር ነው።በስውር ያሰሩት፣የገደሉት እና የሰወሩት ሕዝብ ቁጥር አሁን መናገር አንችልም። ምክንያቱም ሁሉን በድብቅ ነው የሚያደርጉት" ካሉ በኃላ ስለመጭዋ ኢትዮጵያ ማሰብ እንደሚገባ እና እርሳችውንም የሚያሳስባቸው ጉዳይ መሆኑን ጠቅሰዋል።ለዚህም የሱማሌ፣ደቡብ ሱዳን ጉዳይ እያነሱ በሰፊው ለማብራራት ሞክረዋል። አቶ ሌንጮ ኢትዮጵያ እስካሁን እንደ ሀገር እንድትቆይ ካደረጋት ጉዳይ ውስጥ ቀዳሚው ያሉት የህዝቡ ጨዋነት መሆኑን ሲናገሩ እንዲህ አሉ - "ኢትዮጵያን እስካሁን ጠብቆ ያኖራት የህዝቧ ጨዋነት እንጂ የመሪዎቿ ብቃት አይደልም" ነበር ያሉት።በመቀጠልም አቶ ሌንጮ አሁን ያለው መንግስትም ሆነ ተቃዋሚዎች እንዲሁም ሕዝቡም ትኩረት የማይሰጠው ጉዳይ የህዝብ ቁጥር መጨመር እና እርሱን ተያይዞ የሚመጣው የአካባቢ ብክለት፣ የማህበራዊ ኑሮ መዳከም እና የህዝብ ኑሮ ማሽቆልቆል ዋነኞቹ ችግሮች ውስጥ እንደሚካተት አብራርተዋል።
ከጉባኤው ተሳታፊዎች በከፊል 
በመቀጠል ንግግር ያደርጉት ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የአርበኞች ግንቦት 7 ሊቀመንበር ነበሩ።ፕሮፌሰሩ ንግግራቸውን የጀመሩት ሶስት ነገሮችን በቅድምያ ካላወቅን ነገን ለማወቅ ያስቸግረናል በሚል መነሻ ነጥቦች ነበር። እነርሱም : -
1/ አሁን የገጠመን ባላንጣ (የወያኔ ስርዓት) ብሔራዊ ጥቅም የሚባል ነገር የማያውቅ፣ ስርዓቱ ስልጣኑን የማያስጠብቅበት ሁኔታ ከተፈጠረ ሁሉ ነገር እንዲወድም የሚሰራ ስርዓት መሆኑን፣
2/ የሀገራችን ፖለቲካ  በብዙ ምክንያቶች ውስብስብ ችግሮች ውስጥ ያለ መሆኑ እና 
3/ የህዝባችን የሞራል ደረጃ እየወረደ መምጣቱ የሚሉት መሆናቸውን አብራርተዋል።
ከላይ ለተጠቀሱት ችግሮች የአገር አድን ንቅናቄው መፍትሄ መሆኑን ለማመላከት ንቅናቄው እንዴት ችግሮች ይፈታሉ ብሎ እንደሚሰራ አብራርተዋል።
ለመሆኑ የአገር አድን ንቅናቄው ለኢትዮጵያ የፖለቲካ ችግሮች የሚሰጣቸው ስልታዊ ምንድን ናቸው? በሚል በጥያቄ ንግግራቸውን የቀጠሉት ፕሮፌሰር ብርሃኑ ንቅናቄው በሚከተሉት ስልታዊ መንገድ የኢትዮጵያን የፖለቲካ ችግር የመፍታት አቅም እንዳለው አብራርተዋል።
1/ በሚደረጉ የንቅናቄው ውይይቶች መጥራት የሚጎዳላቸው የሃጋራችን የፖለቲካ ችግሮች እንዲጠሩ በማድረግ፣ 
2/ በውይይቱ ሂደት መስማማት።በሂደቱ ላይ ከተስማማን በውጤቱ ላይ መስማማት መጨረሻ የሚመጣ ጉዳይ ነው። አሁን የውይይቱ ሂደት ዲሞክራሲያዊ መሆኑ ላይ መስማማት እና ውጤቱን ደግሞ ሕዝብ እንዲወስን መተው ነው።
በዲሞክራሲ ሂደት ላይ ከተስማማን በሌሎች ጉዳዮች ላይ ልዩነት አይኖርም ማለት አይደለም።ለምሳሌ በኢኮኖሚ ጉዳዮች ላይ እና በሌሎች በርካታ ጉዳዮች ላይ የግድ ላንስማማ እንችላለን። ሆኖም  ግን የቀሪ ልዩነታችን መፍቻ ዲሞክራሲያዊ አፈታትን ስለመረጥን ብዥታ አይኖርም  ማለት ነው።
ለጨረታ የቀረበው እና ከበርገን ከተማ የመጡ የጉባኤ ታዳሚዎች በ13 ሺህ የኖርዌይ ክሮነር የወሰዱት ስዕል 
ከእዚህ በተጨማሪ የጋራ ንቅናቄው ምን እያደረገ ነው? ለሚሉ ጥያቄዎች  ፕሮፌሰር ብርሃኑ ሲያስረዱ አገራዊ ንቅናቄው - 
ሀ) ዋና ጉዳዮች ላይ ማትኮር መቻሉ ፣
ለ) ሌሎች ድርጅቶችን እያሰባሰበ ወደ አንድ ነጥብ ማምጣት ላይ እየሰራ መሆኑ፣
ሐ) ድርጅቶችን ማቀፉ የትግሉን መልክአ ምድራዊ ሽፋን ማስፋቱ እና አገራዊ ቅርፅ መያዙ፣ የሚሉት ተጠቃሽ ናቸው። 
ፕሮፌሰር ብርሃኑ ከላይ የተጠቀሱትን ሶስት የንቅናቄው ተግባራት በምሳሌ ካስረዱ በኃላ የወያኔን ውድቀት ለማፋጠን የሚያስፈልጉ ሶስት አበይት ጉዳዮችን ጠቅሰዋል። እነርሱም -
1ኛ) የጠራ መንገድ በትግሉ ሂደት መያዝ፣
2ኛ) መሬት የያዘ ትግል ማካሄድ እና 
3ኛ) ወያኔ ያዳከመብንን ሞራላዊ ልዕልና መልሰን መገንባት እና ማምጣት የሚሉ ናቸው።
ከላይ የተጠቀሱት ሶስት አበይት ጉዳዮች ውስጥ የሞራል ልዕልናችንን መልሰን መገንባት የእረጅም ጊዜ ስራችን መሆን ያለበት ሲሆን ቀሪዎቹ ሁለቱ ግን በፍጥነት የሚሰሩ እና አሁን እያከናወናቸው ያሉ ስራዎች መሆናቸውን አውስተዋል።
በእዚሁ ጉባኤ ላይ ከነበሩት የፕሮፌሰር ብርሃኑ እና አቶ ሌንጮ ንግግሮች በተጨማሪ የጥያቄ እና መልስ መርሃ ግብር ነበር።በጥያቄ ከተነሱት ውስጥ አሁን ያለነው ወጣቶች በወያኔ ዘመን ያደግን ስለሆነ ስለ ጎጥ እየሰማን ስላደግን ኢትዮጵያዊ ስሜታችን ሳይጎዳ ለመጠበቅ ምን ማድረግ ´አለብን? የሚል የነበረ ሲሆን አቶ ሌንጮ ሲመልሱ - 
"በኢትዮጵያ ታሪክ ማንም ንጉስ ከእዚህ ብሔር የመጣሁ ነኝ ብሎ አያውቅም።በኢትዮጵያም  ጨቋኝ  የሚባል ብሔር የለም።የጨቆነ ከአንድ ብሔር የወጣ ቡድን ቢሆን ይህ ቡድን ብሄሩን ይወክላል ማለት አለመሆኑ ሊሰመርበት ይገባል።" ብለዋል።በመጨረሻም አቶ ሌንጮ " እኔ ኦሮሞም ኢትዮጵያዊም መሆን እፈልጋለሁ።" ብለዋል። በማስከተልም ፕሮፌሰር ብርሃኑ ኢትዮጵያዊነት ከኢትዮጵያዊው ወጣት ትውልድ ውስጥ ወጥቷል የሚል ፈፅሞ ግምት እንደሌላቸው እና ለእዚህም በርካታ  ማስረጃዎች መኖራቸውን አብነት እየጠቀሱ አስረድተዋል።
በመጨረሻም በዋናነት የፕሮፌሰር ብርሃኑን እና አቶ ሌንጮ ለታን ንግግር፣ከህዝብ የተነሱ ጥያቄዎች መመለስ፣የገቢ ማሰባሰቢያ ጨረታ የተካሄደበት ጉባኤ ከምሽቱ 4 ሰዓት ላይ እንግዶችን በክብር በመሸኘት ተፈፅሟል።ባጠቃላይ በእዚህ ጉባኤ ላይ የታየው ከፍተኛ ዲስፕሊን፣የሰዓት አጠቃቀም እና የመድረክ መስተንግዶ ሁሉ የተዋጣለት እና ደረጃውን የጠበቀ መሆን የጉባኤውን ተሳታፊዎችንም ሆነ እንግዶችን ያስደሰተ ተግባር ሆኖ አምሽቷል።

Thursday, June 15, 2017

ጋዜጠኛ ውብሽት ታዬ ለሰበር ሰሚ ችሎት አቤቱታ አቀረበ

አውራምባ ታይምስ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ ሆኖ ይሰራ የነበረው ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ 2003ዓም ሰኔ ወርላይ ከሌሎች 4 ሰዎች ጋር (ጋዜጠኛ ኤልያስ ክፍሌ፣ ጋዜጠኛ ርዕዮት ዓለሙ፣ ዘሪሁን /እግዚአብሄር እናሂሩት ክፍሌየፀረ ሽብርተኝነት ህጉን ተላልፈሃል ተብሎ ክስ ተመስርቶበት የነበረ መሆኑን እና 14 አመት የእስር ቅጣት እንደተወሰነበት የሚታወስ ነው።

ቅጣቱ ከተላለፈበት በኋላ ጥፋተኛ መባሉን በመቃወም ጠቅላይ /ቤት ይግባኝ ቢልም መዝገቡበይቅርታ ጉዳይ እየታየ መሆኑ ተገልፆለት በወቅቱ ይግባኝ ማለት ሳይችል ቀርቷል። ከእርሱ ጋር የይቅርታጥያቄ ያቀረቡ የስዊድን ጋዜጠኞች እና በተመሳሳይ መዝገብ የምትገኘው ሂሩት ክፍሌ ከእስር የተለቀቁሲሆን፤ የጋዜጠኛ ውብሸት የይቅርታ ጉዳይ ግን እስካሁን ድረስ ተፈፃሚ አልሆነም።

በመሆኑም በቅርቡ በወንጀለኛ መቅጫ ስነስረአት ህጉ አንቀፅ 191 ስር በተመለከተው መሰረት የይግባኝጊዜ ካለፈ በኋላ ይግባኝ ለማቅረብ ፈቃድ ለማግኘት የሚቀርብ ማመልከቻ በማስገባት ጠቅላይ /ቤትይግባኙን አቅርቦ ነበር። የወንጀለኛ መቅጫ ስነስርአት ህጉ አንቀፅ 196 (1) እና (2) የተፈረደባቸው ብዙሰዎች ሆነው አንዱ ብቻ ይግባኝ ያቀረበ እና የተጠቀመ [ከእርሱ ጋር አብራ የተከሰሰችው ጋዜጠኛርዕዮት አለሙ ከጋዜጠኛ ውብሸት ጋር ተመሳሳይ የቀረበባት እነወዲሁም የስር /ቤት 14 ዓመትከፈረደባት በኋላ በይግባኝ ወደ 5 አመት እንደተቀነሰላት ይታወቃል።እንደሆነ ሌሎቹም ይግባኝእንዳሉ እንደሚቆጠር እንደሚደነግግ በመጥቀስ ነው ይግባኙን ያቀረበው። ይግባኙን የተመለከተውይግባኝ ሰሚ ችሎት የይግባኙን አቤቱታ ሳይቀበለው ውድቅ አድርጎበታል። ጋዜጠኛ ውብሸትም ይግባኝሰሚ ችሎት መሰረታዊ የህግ ስህተት በመጣስ ይግባኙን እንዳልተቀበለው በመግለፅ ያቀረበው አቤቱታዛሬ ሰበር ሰሚ ችሎት ቀርቦ ነበር። ዳኞች ጉዳዩን መርምረው ብይኑን ሰኔ 12/2009 ቀን እንደሚያደርሱእና ውሳኔውን ከመዝገብ ቤት ከማግኘት እንደሚቻል ተናግረዋል።

ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ 2007 “የነፃነት ድምፆች” እና “ሞጋች እውነቶች” የተሰኙ መፅሐፍት ለንባብያበቃ ሲሆን በመጪው ሰኞ ሰኔ 12/2009 ቀን ከታሰረ 6ዓመት ይሞላዋል።


ምንጭ-  የኢትዮጲያ ሰብዓዊ መብቶች ፕሮጀክት

Tuesday, April 25, 2017

ህዝባዊ ወያኔ አርነት ትግራይ በውስጡ ያለው ቅራኔ ከፍተኛ ደረጃ መድረሱ ታወቀ።

ህዝባዊ ወያኔ አርነት ትግራይ በውስጡ ያለው ቅራኔ ከፍተኛ ደረጃ መድረሱን እና አስታራቂዎችን እስከመማፀን እንደደረሰ አስተማማኝ መረጃ እንደደረሰው የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቭዥን ሚያዝያ 16፣2009 ዓም ፣ምሽት ባስተላለፈው የአጭር ሞገድ ራድዮ ፕሮግራሙ ላይ ገልጧል።ክፍፍሉ ኢትዮጵያን በመጠኑ በተሰጠ መብት እንግዛ ወይንስ በአዋጁ መሰረት ማሰርና በመግደል እንቀጥል? በሚል ልዩነት መሆኑን ለማወቅ ተችሏል።

በሌላ በኩል የክፍፍሉ መነሻ በአስተዳደር ጉዳይ ላይ ብቻ ሳይሆን ከሀገሪቱ በተዘረፈ ጉዳይ ዙርያ የሁሉም እጅ ከመኖሩ አንፃር አንዱ ከአንዱ የተሻለ መሆኑን ለማሳየት የሚደረግ ጥረት እና በእዚሁም ሳብያ አንድኛው ቡድን ሌላውን ለማሰር ከማሰብ የተነሳ እንደሚሆን ሲነገር ሰንብቷል።

ኢሳት በራድዮ ፕሮግራሙ ላይ እንደገለፀው ክፍፍሉን ተከትሎ በሕወሓት በእራሱ በተመረጡ የገለልተኛ ቡድን ደረግ የነበረው ሽምግልና ፍሬ ባለማስገኘቱ አትሌት ኃይሌ ገብረ ስላሴ፣ ፕሮፌሰር ኤፍሬም ይስሐቅ፣ የኢትዮጵያ ጥናታዊ አርበኞች ሊቀ መንበር ልጅ ዳንኤል ጁቴ እና ነጋዴዎችን ያካተተ መሆኑ ተሰምቷል።

የክፍፍሉ አሰላለፍ

1ኛ/ በጀነራል ሳሞራ የኑስ የሚመራው ስር የሚገኙ : –

  – በወታደራዊ መረጃ ኃላፊ ሜጀር ጀነራል ገብሬ ዲላ ፣

 – የሜቴከ (ብረታብረት ኢንጂነሪንግ) ኃላፊ,

– የትግራይ ክልል ፕሬዝዳንት አቶ አባይ ወልዱ እና

– የአቶ መለስ ባለበት ወ/ሮ አዜብ መስፍን ሲገኙበት

2ኛ/ በአቦይ ስብሐት የሚመራው ቡድን ስር የሚገኙ : –

 – አቶ አባይ ፀሐዬ እና

 – የደህንነት ኃላፊው አቶ ጌታቸው አሰፋ እንደሚገኙ ለማወቅ ተችሏል።

3ኛ/ ዶ/ር ደብረ ፅዮን እና ዶ/ር አርከበ እስካሁን ከየትኛው ቡድን እንደተሰለፉ አልታወቅም።

የኢትዮጵያ አምላክ ይፈርዳል ሳይውል ሳያድር

በድምፃዊ ኃይልዬ ታደሰ

Thursday, April 20, 2017

ድርቁ በተለያዩ የሃገሪቱ ክፍሎች የከፋ ጉዳት እያደረሰ እንደሚገኝ በ አለም አቀፍ ድርጅቶች ተገለጸ

የድርቅ አደጋ ለመከላከል ከሚያስፈልገው የአንድ ቢሊዮን ዶላር ድጋፍ መካከል 23 ሚሊዮን ዶላር ብቻ መገኘቱ ተገለጸ
ኢሳት (ሚያዚያ 12 ፥ 2009)
በኢትዮጵያ ተከስቶ ያለውን የድርቅ አደጋ ለመከላከል ከአለም አቀፉ ማህበረሰብ ከሚያስፈልገው የአንድ ቢሊዮን ዶላር ድጋፍ መካከል 23 ሚሊዮን ዶላር ብቻ መገኘቱ ተገለጸ።
የአለም አቀፍ ማህበረሰብ ወቅታዊ ምላሽ አለመስጠቱን ተከትሎ ድርቁ በተለያዩ የሃገሪቱ ክፍሎች የከፋ ጉዳት እያደረሰ እንደሚገኝ የተባበሩት መንግስታት እና አለም አቀፍ የዕርዳታ ድርጅቶች አስታውቀዋል።
ባለፈው አመት በሃገሪቱ ተከስቶ የነበረውን ተመሳሳይ የድርቅ አደጋ ከመንግስትና ከአለም አቀፉ ማህበረሰብ የተሻለ ድጋፍ ተገኝቶ እንደነበር ያወሳው ወርልድ ቢዥን በዘንድሮው አመት የተከሰተው የድርቅ አደጋ ለመከላከ ግን ከሁለቱም ወገኖች የበጀት ጉድለቱ ከፍተኛ ሆኖ መቀጠሉን የሰብዓዊ ዕርዳታ ተቋሙን ዋቢ በማድረግ የተባበሩት መንግስታት የሰብዓዊ ሚድያ አውታር (ኢሪን) ዘግቧል።
የወርልድ ቪዥን የኢትዮጵያ ተወካይ የሆኑት ኤድዋርድ ብራውን አሜሪካንን ጨምሮ የተለያዩ ሃገራትና አለም አቀፍ ተቋማት ለአለም አቀፍ እርዳታ የሚሰጡትን ድጋፍ በመቀነስ ላይ በመሆናቸው ድርቁን በመከላከል ዘመቻውን ላይ ተፅዕኖ እያሳደረ መሆኑን አስረድተዋል።
በሃገሪቱ ዳግም ተከስቶ ያለው የድርቅ አደጋ መንግስት ለመከላከል እያካሄደ ባለው ዘመቻ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ እያሳደረ መሆኑን ሃላፊው ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ የሶማሌ ክልል በ222 ጊዜያዊ መጠለያዎች 400ሺ አካባቢ የሚጠጉ ከመኖሪያ ቀያቸው የተፈናቀሉ ተረጂዎች ቢኖሩም በ58 ጣቢያዎች ብቻ ያሉት ከመንግስት ድጋፍ እያገኙ መሆኑን የዜና አውታሩ በዘገባው አቅርቧል።
ከ222ቱ መጠለያዎች መካከል 44 በመቶ የሚሆኑ የምግብ ድጋፍ እንደሚያገኙ የተገለጸ ሲሆን፣ ድርቁ በእስካሁኑ ቆይታው 200 ሚሊዮን ዶላር (ከአራት ቢሊዮን ብር) በላይ የሚገመት የእንስሳት ሞት ማስከተሉም ኢሪን አመልክቷል። በአራት ክልሎች ተከስቶ ያለው የድርቅ አደጋ በተለይ በኢትዮጵያ የሶማሌ ክልል በነዋሪዎች ላይ የከፋ ጉዳት እያደረሰ መሆኑ ይነገራል።
የምግብ እጥረቱ እያደረሰ ካለው ጉዳት በተጨማሪ የኮሌራ በሽታ ወረርሽኝ በሰዎች ህይወት ላይ ጉዳት እያደረሰ መሆኑ በተደጋጋሚ ሲገለፅ ቆይቷል።
በሶማሌ ክልል ከፍተኛ ጉዳት እያደረሰ ያለው የድርቅ አደጋ 40 በመቶ አካባቢ የሚሆን የአካባቢውን እንስሳት እንደጨረሰ የተባበሩት መንግስታት የምግብና እርሻ ድርጅት መረጃ ያመለክታል። በተለይ በሶማሌ ክልል የእንስሳት ሃብታቸውን ያጡ አርብቶ አደሮች ከድርቁ ሙሉ ለሙሉ ለማገገም እስከ 10 አመት እንደሚፈጅባቸውም ተመልክቷል።
በተያዘው አመት የበልግ ወቅት በአብዛኛው የሃገሪቱ አካባቢ መጣል የነበረበትን ዝናብ በተጠበቀው መጠን ባለመጣሉ ምክንያት ድርቁ እስከቀጣዩ አመት ድረስ ቀጣይ እንደሚሆን ተሰግቷል።
መንግስት የአስቸኳይ ጊዜ የምግብ ተርጂዎችን ቁጥር እየጨመረ በመሄድ ላይ መሆኑን በቅርቡ ቢያረጋግጥም ቁጥሩን ግን ከመግለጽ ተቆጥቧል።
መንግስትና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት 5.6 ሚሊዮን ለሚሆኑ ተረጂዎች አንድ ቢሊዮን ዶላር አካባቢ እንደሚያስፈልግ ከወራት በፊት ይፋ ማድረጋቸው ይታወሳል። ይሁንና በእስከ አሁኑ ቆይታ 23.7 ሚሊዮን ዶላር ብቻ መገኘቱ ይፋ ተደርጓል።
በተያያዘ ዜና፣ የብሄራዊ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽነር አቶ ምትኩ ካሳ መንግስት የድርቅ አደጋውን በራሱ እየተቋቋመ ነው ሲሉ ሃሙስ ለሃገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን አስታውቀዋል።
ይሁንና የውጭ የእርዳታ ድርጅቶች እና ሃገራት የሚያደርጉት ድጋፍ አናሳ በመሆኑ ድጋፋቸውን ሊያጠናክሩ ይገባል ሲሉ ሃላፊው ጥሪን አቅርበዋል።
ድርቁን ለመታደግ ወደ አንድ ቢሊዮን ዶላር አካባቢ እንደሚያስፈልግ ጥሪ ቢደረግም 93 ሚሊዮን ዶላር ብቻ ተገኝቷል ሲሉ አቶ ምትኩ አክለው ገልጸዋል።
መንግስት ድርቁን ለመታደግ ተገኝቷል ያለው ገንዘብ የእርዳታ ድርጅቶች ካስታወቁት ጋር የ69 ሚሊዮን ዶላር አካባቢ ልዩነት እንዳለው ታውቋል።
የውጭ ሃገር የእርዳታ ተቋማት ለተለያዩ የሰብዓዊ ዕርዳታ የያዙትን በጀት በሶማሌ ክልል ተከስቶ ላለው የኮሌራ በሽታ ወረርሽኝ እንዲያዞሩት መጠየቃቸው አይዘነጋም።

Ethiopia says 669 killed in months of violent protestsApr 18, 2017

Ethiopia says 669 killed in months of violent protestsApr 18, 2017
ADDIS ABABA, Ethiopia (AP) — Months of violent protests that sparked Ethiopia’s current state of emergency left at least 669 people dead but security forces used “proportionate measures” to counter the unrest, the government-affiliated Ethiopian Human Rights Commission said Tuesday.
The protests that began in November 2015 and spreadApr 18, 2017
ADDIS ABABA, Ethiopia (AP) — Months of violent protests that sparked Ethiopia’s current state of emergency left at least 669 people dead but security forces used “proportionate measures” to counter the unrest, the government-affiliated Ethiopian Human Rights Commission said Tuesday.
The protests that began in November 2015 and spread throughout the country demanding wider political freedoms posed a challenge to one of Africa’s fastest-growing economies and a government accused by human rights groups of suppressing dissenting voices.
The commission’s report to lawmakers largely blamed opposition groups for what it called illegal rallies in the restive Oromia and other regions. But it also said security forces were not properly prepared for a protest that turned into a deadly stampede in October and sparked the state pf emergency declaration.
Lawmakers in March extended the six-month state of emergency for another four months.
Human rights groups have accused Ethiopia’s government of carrying out extrajudicial killings during the protests and have urged independent investigations.
The human rights commission’s report recommended that security forces at fault in a number of incidents across the country should be brought to justice.
Betsate Terefe, the executive director of the independent Human Rights Council, said sample studies conducted in 33 out of 350 localities in the Oromia region indicated that 103 extrajudicial killings were carried out during the months of protests.
“Imagine, this is in just 33 localities in one region alone. I leave it for you to imagine what the total figure will be if we conducted the investigations in all the localities of all the affected the regions,” he told The Associated Press.
More than 25,000 people suspected of taking part in protests were detained under the state of emergency. Several thousand have been released. The government has indicated that a “few thousand” will face justice for organizing protests.
Ethiopia media forum (EMF)