ዳንኤል ፍቅሬ
የሕወሓት አገዛዝን በመደገፍ አሊያም በመተባበር ብቻ ነፃነት አለ፡፡ ህወሓት በፈለገው ሰዓት የፈለገውን አጀንዳ ቀርፆ ድጋፍ እንዲደረግለት በግዳጅና በአነስተኛ የውሎ አበል ክፍያ ሰልፍ በመውጣት “ነፃነት” አለ፡፡
አገዛዙን በመተቸት እና ስለህዝቡና ስለ ሀገራችን ያገባናል በሚል የሕወሓትን ብልሹ አሰራር የተቃወሙትን እስር በመደገፍ በየቀበሌውና በየአዳራሹ ተስብስቦ እስሩን በመደገፍ “ነፃነት” አለ፡፡ የአገዛዙ ጠብደል ሹማምንት የህዝቡን እና የሀገሪቱን ጥቅም ያለ ተጠያቂነት እና ኃላፊነት ሲፈልጉ እንዳሻቸው አሊያም ለሌላ ሶስተኛ አካል በፍላጎታቸው ልክ ሲቸሩ ዝም በማለት “ነፃነት” አለ፡፡
የሕወሓትን ድርጊት ለመደገፍ አሊያም በዝምታ በማለፍ “የፕሬስ ነፃነት” አለ፡፡ ይሄ ነው የዛሬዋ የሕወሓቷ ኢትዮጵያ ዴሞክራሲ፣ የፕሬስ ነፃነት፣ ፍትህ እና ሐሳብን በነፃነት የመግለፅ መብት፡፡ በዜጎች ላይ የሚፈፀመውን ግፍ ለመቃወምና ለማጋለጥ፣ የተሻለ አማራጭ ሐሳብ ማንሳት፣ ዜጎች ሌላው ሰው ሳይጎዳ ያመኑበት እና የመረጡት ሐሳብ ማንሳት አሊያም ማራመድ፣ ለሀገርና ለወገን መቆረቆር እንደወንጀል ተቆጥሮ በሐሰት ክስ በሕወሓት አሰቃቂ ማጎሪያዎችና የካንጋሮ ፍርድ ቤት ለመንከራተት ተገደዋል።
![](https://3.bp.blogspot.com/-bZf6m0Bc-OI/VwMKtSo4fOI/AAAAAAAACak/R1jFm4vJQpo3jGxQ5MMjeOMRQbXD5ufYQ/s400/free%2Ball%2Bp.jpg)
ፍትህ፣ ነፃነት እና እኩልነት ለሁሉም ዜጎች!!
#Free All Prisoners Of Conscience! #Free Journalists! #Free Bloggers!#FreePoliticians! #FreeEthiopia!