ከጁመአ ሰላት ጋር በተያያዘ የተቃውሞ መርሃ ግብር ነበር በስፍራው የተለያዩ በራሪ ወረቀቶች እና መፈክሮች ነበሩ ::
ከነዚህ መካከል <<የታሰሩት ይፈቱ>> ፣ <<ድምፃችን ይሰማ >>፣ <<የሃይማኖት ነፃነትን ማክበር ግዴታ እንጂ መብት አይደለም >> የሚሉ እና ሌሎች መፈክሮችም ነበሩ ፡፡
የጁመአ ሰላት ሁለት ረከአ (ሁለት ጊዜ) የሚሰገድ ሰላት ነው ፡፡ ነገር ግን ብትላንትናው እለት ተሰግዶ ሳይገባደድ ማለትም አንደኛው ረከአ ላይ ብጥብጥ ሊፈጠር ችሏል፡፡
የጁመአ ሰላት ሁለት ረከአ (ሁለት ጊዜ) የሚሰገድ ሰላት ነው ፡፡ ነገር ግን ብትላንትናው እለት ተሰግዶ ሳይገባደድ ማለትም አንደኛው ረከአ ላይ ብጥብጥ ሊፈጠር ችሏል፡፡
ውጥረቱ ቀጥሏል በስፍራው ከነበሩ እማኞች መረዳት የሚቻለውም በተደጋጋሚ የቶክስ ድምፅ ተሰምቷል ፡፡
በወርሃ ረመዳን ላይ ይገኛል የሙስሊሙ ማህበረሰብ (በእስልምና እምነት ውስጥ ትልቁ የጾም ወር ነው) እንዲህ አይነት ነገር ሲከሰት ለመጀመሪያ ጊዜ አልነበረም የዛሬ ሁለት አመት 2004 ክረምት ላይ በዚሁ የፆም ወቅት ተመሳሳይ ነገር ተፈጥሮ ነበር ፡፡
ባለፈው አመት ደግሞ በኢድ አልፈጥር በአል ቀን ከስግደት መልስ የተፈጠሩ ነገሮች እንደነበሩ ይታወሳል፡፡
በትላንትናው እለትም ጉዳት የደረሰባቸው የፖሊስ አአባላት እና እንዲሁም ቁጥራቸው በውል የማይታወቅ በርከት ያሉ የእምነቱ ተከታዮች የደረሰባቸውን ጉዳት በአካባቢው ወደሚገኙ መካከለኛ ክሊኒኮች እና ሆስፒታሎች እርዳታ እንደተደረገላቸው ነው።








.png)