Thursday, June 15, 2017

ጋዜጠኛ ውብሽት ታዬ ለሰበር ሰሚ ችሎት አቤቱታ አቀረበ

አውራምባ ታይምስ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ ሆኖ ይሰራ የነበረው ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ 2003ዓም ሰኔ ወርላይ ከሌሎች 4 ሰዎች ጋር (ጋዜጠኛ ኤልያስ ክፍሌ፣ ጋዜጠኛ ርዕዮት ዓለሙ፣ ዘሪሁን /እግዚአብሄር እናሂሩት ክፍሌየፀረ ሽብርተኝነት ህጉን ተላልፈሃል ተብሎ ክስ ተመስርቶበት የነበረ መሆኑን እና 14 አመት የእስር ቅጣት እንደተወሰነበት የሚታወስ ነው።

ቅጣቱ ከተላለፈበት በኋላ ጥፋተኛ መባሉን በመቃወም ጠቅላይ /ቤት ይግባኝ ቢልም መዝገቡበይቅርታ ጉዳይ እየታየ መሆኑ ተገልፆለት በወቅቱ ይግባኝ ማለት ሳይችል ቀርቷል። ከእርሱ ጋር የይቅርታጥያቄ ያቀረቡ የስዊድን ጋዜጠኞች እና በተመሳሳይ መዝገብ የምትገኘው ሂሩት ክፍሌ ከእስር የተለቀቁሲሆን፤ የጋዜጠኛ ውብሸት የይቅርታ ጉዳይ ግን እስካሁን ድረስ ተፈፃሚ አልሆነም።

በመሆኑም በቅርቡ በወንጀለኛ መቅጫ ስነስረአት ህጉ አንቀፅ 191 ስር በተመለከተው መሰረት የይግባኝጊዜ ካለፈ በኋላ ይግባኝ ለማቅረብ ፈቃድ ለማግኘት የሚቀርብ ማመልከቻ በማስገባት ጠቅላይ /ቤትይግባኙን አቅርቦ ነበር። የወንጀለኛ መቅጫ ስነስርአት ህጉ አንቀፅ 196 (1) እና (2) የተፈረደባቸው ብዙሰዎች ሆነው አንዱ ብቻ ይግባኝ ያቀረበ እና የተጠቀመ [ከእርሱ ጋር አብራ የተከሰሰችው ጋዜጠኛርዕዮት አለሙ ከጋዜጠኛ ውብሸት ጋር ተመሳሳይ የቀረበባት እነወዲሁም የስር /ቤት 14 ዓመትከፈረደባት በኋላ በይግባኝ ወደ 5 አመት እንደተቀነሰላት ይታወቃል።እንደሆነ ሌሎቹም ይግባኝእንዳሉ እንደሚቆጠር እንደሚደነግግ በመጥቀስ ነው ይግባኙን ያቀረበው። ይግባኙን የተመለከተውይግባኝ ሰሚ ችሎት የይግባኙን አቤቱታ ሳይቀበለው ውድቅ አድርጎበታል። ጋዜጠኛ ውብሸትም ይግባኝሰሚ ችሎት መሰረታዊ የህግ ስህተት በመጣስ ይግባኙን እንዳልተቀበለው በመግለፅ ያቀረበው አቤቱታዛሬ ሰበር ሰሚ ችሎት ቀርቦ ነበር። ዳኞች ጉዳዩን መርምረው ብይኑን ሰኔ 12/2009 ቀን እንደሚያደርሱእና ውሳኔውን ከመዝገብ ቤት ከማግኘት እንደሚቻል ተናግረዋል።

ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ 2007 “የነፃነት ድምፆች” እና “ሞጋች እውነቶች” የተሰኙ መፅሐፍት ለንባብያበቃ ሲሆን በመጪው ሰኞ ሰኔ 12/2009 ቀን ከታሰረ 6ዓመት ይሞላዋል።


ምንጭ-  የኢትዮጲያ ሰብዓዊ መብቶች ፕሮጀክት

Tuesday, April 25, 2017

ህዝባዊ ወያኔ አርነት ትግራይ በውስጡ ያለው ቅራኔ ከፍተኛ ደረጃ መድረሱ ታወቀ።

ህዝባዊ ወያኔ አርነት ትግራይ በውስጡ ያለው ቅራኔ ከፍተኛ ደረጃ መድረሱን እና አስታራቂዎችን እስከመማፀን እንደደረሰ አስተማማኝ መረጃ እንደደረሰው የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቭዥን ሚያዝያ 16፣2009 ዓም ፣ምሽት ባስተላለፈው የአጭር ሞገድ ራድዮ ፕሮግራሙ ላይ ገልጧል።ክፍፍሉ ኢትዮጵያን በመጠኑ በተሰጠ መብት እንግዛ ወይንስ በአዋጁ መሰረት ማሰርና በመግደል እንቀጥል? በሚል ልዩነት መሆኑን ለማወቅ ተችሏል።

በሌላ በኩል የክፍፍሉ መነሻ በአስተዳደር ጉዳይ ላይ ብቻ ሳይሆን ከሀገሪቱ በተዘረፈ ጉዳይ ዙርያ የሁሉም እጅ ከመኖሩ አንፃር አንዱ ከአንዱ የተሻለ መሆኑን ለማሳየት የሚደረግ ጥረት እና በእዚሁም ሳብያ አንድኛው ቡድን ሌላውን ለማሰር ከማሰብ የተነሳ እንደሚሆን ሲነገር ሰንብቷል።

ኢሳት በራድዮ ፕሮግራሙ ላይ እንደገለፀው ክፍፍሉን ተከትሎ በሕወሓት በእራሱ በተመረጡ የገለልተኛ ቡድን ደረግ የነበረው ሽምግልና ፍሬ ባለማስገኘቱ አትሌት ኃይሌ ገብረ ስላሴ፣ ፕሮፌሰር ኤፍሬም ይስሐቅ፣ የኢትዮጵያ ጥናታዊ አርበኞች ሊቀ መንበር ልጅ ዳንኤል ጁቴ እና ነጋዴዎችን ያካተተ መሆኑ ተሰምቷል።

የክፍፍሉ አሰላለፍ

1ኛ/ በጀነራል ሳሞራ የኑስ የሚመራው ስር የሚገኙ : –

  – በወታደራዊ መረጃ ኃላፊ ሜጀር ጀነራል ገብሬ ዲላ ፣

 – የሜቴከ (ብረታብረት ኢንጂነሪንግ) ኃላፊ,

– የትግራይ ክልል ፕሬዝዳንት አቶ አባይ ወልዱ እና

– የአቶ መለስ ባለበት ወ/ሮ አዜብ መስፍን ሲገኙበት

2ኛ/ በአቦይ ስብሐት የሚመራው ቡድን ስር የሚገኙ : –

 – አቶ አባይ ፀሐዬ እና

 – የደህንነት ኃላፊው አቶ ጌታቸው አሰፋ እንደሚገኙ ለማወቅ ተችሏል።

3ኛ/ ዶ/ር ደብረ ፅዮን እና ዶ/ር አርከበ እስካሁን ከየትኛው ቡድን እንደተሰለፉ አልታወቅም።

የኢትዮጵያ አምላክ ይፈርዳል ሳይውል ሳያድር

በድምፃዊ ኃይልዬ ታደሰ

Thursday, April 20, 2017

ድርቁ በተለያዩ የሃገሪቱ ክፍሎች የከፋ ጉዳት እያደረሰ እንደሚገኝ በ አለም አቀፍ ድርጅቶች ተገለጸ

የድርቅ አደጋ ለመከላከል ከሚያስፈልገው የአንድ ቢሊዮን ዶላር ድጋፍ መካከል 23 ሚሊዮን ዶላር ብቻ መገኘቱ ተገለጸ
ኢሳት (ሚያዚያ 12 ፥ 2009)
በኢትዮጵያ ተከስቶ ያለውን የድርቅ አደጋ ለመከላከል ከአለም አቀፉ ማህበረሰብ ከሚያስፈልገው የአንድ ቢሊዮን ዶላር ድጋፍ መካከል 23 ሚሊዮን ዶላር ብቻ መገኘቱ ተገለጸ።
የአለም አቀፍ ማህበረሰብ ወቅታዊ ምላሽ አለመስጠቱን ተከትሎ ድርቁ በተለያዩ የሃገሪቱ ክፍሎች የከፋ ጉዳት እያደረሰ እንደሚገኝ የተባበሩት መንግስታት እና አለም አቀፍ የዕርዳታ ድርጅቶች አስታውቀዋል።
ባለፈው አመት በሃገሪቱ ተከስቶ የነበረውን ተመሳሳይ የድርቅ አደጋ ከመንግስትና ከአለም አቀፉ ማህበረሰብ የተሻለ ድጋፍ ተገኝቶ እንደነበር ያወሳው ወርልድ ቢዥን በዘንድሮው አመት የተከሰተው የድርቅ አደጋ ለመከላከ ግን ከሁለቱም ወገኖች የበጀት ጉድለቱ ከፍተኛ ሆኖ መቀጠሉን የሰብዓዊ ዕርዳታ ተቋሙን ዋቢ በማድረግ የተባበሩት መንግስታት የሰብዓዊ ሚድያ አውታር (ኢሪን) ዘግቧል።
የወርልድ ቪዥን የኢትዮጵያ ተወካይ የሆኑት ኤድዋርድ ብራውን አሜሪካንን ጨምሮ የተለያዩ ሃገራትና አለም አቀፍ ተቋማት ለአለም አቀፍ እርዳታ የሚሰጡትን ድጋፍ በመቀነስ ላይ በመሆናቸው ድርቁን በመከላከል ዘመቻውን ላይ ተፅዕኖ እያሳደረ መሆኑን አስረድተዋል።
በሃገሪቱ ዳግም ተከስቶ ያለው የድርቅ አደጋ መንግስት ለመከላከል እያካሄደ ባለው ዘመቻ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ እያሳደረ መሆኑን ሃላፊው ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ የሶማሌ ክልል በ222 ጊዜያዊ መጠለያዎች 400ሺ አካባቢ የሚጠጉ ከመኖሪያ ቀያቸው የተፈናቀሉ ተረጂዎች ቢኖሩም በ58 ጣቢያዎች ብቻ ያሉት ከመንግስት ድጋፍ እያገኙ መሆኑን የዜና አውታሩ በዘገባው አቅርቧል።
ከ222ቱ መጠለያዎች መካከል 44 በመቶ የሚሆኑ የምግብ ድጋፍ እንደሚያገኙ የተገለጸ ሲሆን፣ ድርቁ በእስካሁኑ ቆይታው 200 ሚሊዮን ዶላር (ከአራት ቢሊዮን ብር) በላይ የሚገመት የእንስሳት ሞት ማስከተሉም ኢሪን አመልክቷል። በአራት ክልሎች ተከስቶ ያለው የድርቅ አደጋ በተለይ በኢትዮጵያ የሶማሌ ክልል በነዋሪዎች ላይ የከፋ ጉዳት እያደረሰ መሆኑ ይነገራል።
የምግብ እጥረቱ እያደረሰ ካለው ጉዳት በተጨማሪ የኮሌራ በሽታ ወረርሽኝ በሰዎች ህይወት ላይ ጉዳት እያደረሰ መሆኑ በተደጋጋሚ ሲገለፅ ቆይቷል።
በሶማሌ ክልል ከፍተኛ ጉዳት እያደረሰ ያለው የድርቅ አደጋ 40 በመቶ አካባቢ የሚሆን የአካባቢውን እንስሳት እንደጨረሰ የተባበሩት መንግስታት የምግብና እርሻ ድርጅት መረጃ ያመለክታል። በተለይ በሶማሌ ክልል የእንስሳት ሃብታቸውን ያጡ አርብቶ አደሮች ከድርቁ ሙሉ ለሙሉ ለማገገም እስከ 10 አመት እንደሚፈጅባቸውም ተመልክቷል።
በተያዘው አመት የበልግ ወቅት በአብዛኛው የሃገሪቱ አካባቢ መጣል የነበረበትን ዝናብ በተጠበቀው መጠን ባለመጣሉ ምክንያት ድርቁ እስከቀጣዩ አመት ድረስ ቀጣይ እንደሚሆን ተሰግቷል።
መንግስት የአስቸኳይ ጊዜ የምግብ ተርጂዎችን ቁጥር እየጨመረ በመሄድ ላይ መሆኑን በቅርቡ ቢያረጋግጥም ቁጥሩን ግን ከመግለጽ ተቆጥቧል።
መንግስትና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት 5.6 ሚሊዮን ለሚሆኑ ተረጂዎች አንድ ቢሊዮን ዶላር አካባቢ እንደሚያስፈልግ ከወራት በፊት ይፋ ማድረጋቸው ይታወሳል። ይሁንና በእስከ አሁኑ ቆይታ 23.7 ሚሊዮን ዶላር ብቻ መገኘቱ ይፋ ተደርጓል።
በተያያዘ ዜና፣ የብሄራዊ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽነር አቶ ምትኩ ካሳ መንግስት የድርቅ አደጋውን በራሱ እየተቋቋመ ነው ሲሉ ሃሙስ ለሃገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን አስታውቀዋል።
ይሁንና የውጭ የእርዳታ ድርጅቶች እና ሃገራት የሚያደርጉት ድጋፍ አናሳ በመሆኑ ድጋፋቸውን ሊያጠናክሩ ይገባል ሲሉ ሃላፊው ጥሪን አቅርበዋል።
ድርቁን ለመታደግ ወደ አንድ ቢሊዮን ዶላር አካባቢ እንደሚያስፈልግ ጥሪ ቢደረግም 93 ሚሊዮን ዶላር ብቻ ተገኝቷል ሲሉ አቶ ምትኩ አክለው ገልጸዋል።
መንግስት ድርቁን ለመታደግ ተገኝቷል ያለው ገንዘብ የእርዳታ ድርጅቶች ካስታወቁት ጋር የ69 ሚሊዮን ዶላር አካባቢ ልዩነት እንዳለው ታውቋል።
የውጭ ሃገር የእርዳታ ተቋማት ለተለያዩ የሰብዓዊ ዕርዳታ የያዙትን በጀት በሶማሌ ክልል ተከስቶ ላለው የኮሌራ በሽታ ወረርሽኝ እንዲያዞሩት መጠየቃቸው አይዘነጋም።

Ethiopia says 669 killed in months of violent protestsApr 18, 2017

Ethiopia says 669 killed in months of violent protestsApr 18, 2017
ADDIS ABABA, Ethiopia (AP) — Months of violent protests that sparked Ethiopia’s current state of emergency left at least 669 people dead but security forces used “proportionate measures” to counter the unrest, the government-affiliated Ethiopian Human Rights Commission said Tuesday.
The protests that began in November 2015 and spreadApr 18, 2017
ADDIS ABABA, Ethiopia (AP) — Months of violent protests that sparked Ethiopia’s current state of emergency left at least 669 people dead but security forces used “proportionate measures” to counter the unrest, the government-affiliated Ethiopian Human Rights Commission said Tuesday.
The protests that began in November 2015 and spread throughout the country demanding wider political freedoms posed a challenge to one of Africa’s fastest-growing economies and a government accused by human rights groups of suppressing dissenting voices.
The commission’s report to lawmakers largely blamed opposition groups for what it called illegal rallies in the restive Oromia and other regions. But it also said security forces were not properly prepared for a protest that turned into a deadly stampede in October and sparked the state pf emergency declaration.
Lawmakers in March extended the six-month state of emergency for another four months.
Human rights groups have accused Ethiopia’s government of carrying out extrajudicial killings during the protests and have urged independent investigations.
The human rights commission’s report recommended that security forces at fault in a number of incidents across the country should be brought to justice.
Betsate Terefe, the executive director of the independent Human Rights Council, said sample studies conducted in 33 out of 350 localities in the Oromia region indicated that 103 extrajudicial killings were carried out during the months of protests.
“Imagine, this is in just 33 localities in one region alone. I leave it for you to imagine what the total figure will be if we conducted the investigations in all the localities of all the affected the regions,” he told The Associated Press.
More than 25,000 people suspected of taking part in protests were detained under the state of emergency. Several thousand have been released. The government has indicated that a “few thousand” will face justice for organizing protests.
Ethiopia media forum (EMF)

Wednesday, December 14, 2016

CPJ ኢትዮፕያ ጋዜጠኞችን በማሰር ከአፍሪካ 3ኛ መሆንዋን ገለፀ

ያለማቀፉ የጋዜጠኞች መበት ተከራካሪ CPJ ኢትዮፕያ ጋዜጠኞችን በማሰር ከአፍሪካ 3ኛ መሆንዋን ገለፀ። የጋዜጠኛ ተመሰገን ደሳለኝ የለበት ሁኔታና ቦታ አለመታወቁም ጨምሮ እንደሚያሳስበው ገልፃል።
https://www.cpj.org/  


Sunday, December 4, 2016

European union are a Terrorist Group?

Ethiopian leader arrested for meeting Brussels bosses

AN ETHIOPIAN opposition leader is being held on terror charges after holding talks with European Union bosses.

Merera Gudina, who leads the Oromo People's Congress, was detained after returning to Addis Ababa from Brussels where he criticised the government in Addis Ababa for imposing a state of emergency.

Mr Gudina has been at the forefront of protests against land grabs in the Oromiya region and what his supporters have described as a government clampdown on political freedoms. 

Wednesday, October 5, 2016

Zone 9 Blogger, Natnael Feleke Arrested 
Yesterday October 04, 2016 Natnael Feleke, a Zone 9 Blogger and two of his friends, Tsedeke Digafe and Addisalem Mulugeta are taken detention. The reason given by the police about their arrest is while sitting at Lalibela Restaurant and talking loudly about the death of hundreds on Sunday, October 02, 2016 at the yearly Thanksgiving ceremony in Bishoftu, Ethiopia and blaming the government for the deaths occurred, they uttered seditious remarks in a public place.
Natnael and his friends brought to the Federal First Instance court, Kera Branch Criminal Bench this morning and the judge adjourned them for tomorrow October 06, 2016 to give a decision on the bail issue.
We at the Zone are deeply saddened by this news that Ethiopia is becoming a country that citizens can’t even discuss anything political. Thus, we request the Ethiopian government to release Natnael and two of his friends unconditionally.
Zone 9