Tuesday, July 29, 2014

ሰበር ዜና አቶ በረከት ስምኦን.........



ሰበር ዜና አቶ በረከት ስምኦን ድፍት እንዳለ ምንጮች አመላከቱ!
ሳውዲ አረቢያ ጅዳ ከተማ ለህክምና የገቡት እኚህ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣን በተለምዶ ብግሻን የሚባል አንድ ትልቅ ሆስፒታል 4 ፎቅ የልብ ቀዶ ጥገና በተሰካ ሁኔታ እንደተደረገላቸው የሚናገሩ ውስጥ፡ አውቂ ምንጮች ከቀዶ ጥገና ክፍሉ ከወጡ በሃላ የባለስልጣኑ የጤንነት ሁኔታ ወደ ነበረበት ሊመለስ ባለመቻሉ ወደሌላ ክፍል ተዘዋውረው የቀርብ ክትትል እየተደረገላቸው መሆኑን ለማወቅ ተችሏል። ይህ በንዲህ እንዳለ አቶ በረከት ስምኦን ወደተኙበት ክፍል ዶክተሮች ባልተለመደ ሁኔታ እየተቻኳሉ ሲገቡ እና ሲወጡ ያዩ የአይን እማኞች የባለስልጣኑንን በህይወት መትረፍ ይጠራጠራሉ።
ከአንድ ቀን በፌት እዚህ ጅዳ ሳውዲ አረቢያ በሼክ አላሙዲን ማካኝነት አንድ ኢትዮጵያዊ ዶክተር አስከትለው ለህክምና እንደገቡ የሚነገረው አቶ በረከት ስምኦን እስካሁን ስላሉበት ሁኔታ በትክከል መናገር ባይቻለም አብረዋቸው ከመጡት የቀርብ ቤተሰቦቻቸው ውስጥ ሚስታቸው እና ሴት ልጃቸው ሆስፒታል ውስጥ ነጠላቸውን ወገባቸው ላይ አስረው ሲላቀሱ ያዩ ታዛቢዎች የባለስልጣኑን በህይወት መኖር ጥያቄ ምልክት ውስጥ እንደከተተው ይነገራል። ለአቶ በረከት አርቴፊሻል የፕላስቲክ ቧንቧ ከልባቸውጋር በድጋፍ የተገጠመ መሆኑን የሚገልጹት የሆስፒታሉ ምንጮችየባለስልጣኑን የልብ መት የሚለካ ግስቲር በተጓዳኝ መገጠሙን እና የልብ ቀዶ ጥገናው በተሳካ ሁኔታ መካሄዱን ያረጋግጣሉ።
አቶ በረከት ስሞኦን ቀደም በልው ድቡብ አፍሪካ ውስጥ ተመሳሳይ የሆነ የልብ ቀዶ ጥገናተደርጎላቸው እንደነበር የሚያሳዩ መረጃዎች ምናልባት በልብ ቀዶ ህክምናው ወቅት ስህተቶች ተፈጥረው በመንግስት ባላስልጣኑ ላይ አደገኛ ኢንፌክሸን ሳይፈጠር እናዳልቀር ይነገራል። አቶ በረከት ስሞን አሁን ስላሉበት የጤንነት ሁኔታ የኢትዮጵያ መንግስት ምንም ያለው ነገር ባይኖረም ስለእህ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣን የጤንነት ሁኔታ ተጨማሪመረጃ ለመስብሰብ በጅዳ የኢትዮጵያ ቆንስላ ጽ/ቤት የሚገኙ አንዳንድ ዲፕሎማቶችን ለማነጋገር ያደረኩት ሙከራ እስካሁን አልተሳካም ።
ምንጭ ታምራት ይደጎ

No comments:

Post a Comment